Friday, 22 May 2015
የወያኔ በጉልበት የምረጡኝ ዘመቻ (ከ አዲስ ብርሃኑ)
ንብን ምረጡ ማለት ከጀመሩ ሰነባብተዋል ። ለአገር እድገት፤ ለብለጽግና ፤ለእኩልነት ፤የተጀመረውን እድገት፤ ለማስቀጠል እያሉ...... እያሉ.... መንገድ ተሰራ፤ ህንጻ ተሰራ ፤ስልጣኔ ገባ ፤ይህን ሁሉ በዘመነ ኢህአዲግ ነው ብለው ይናግሩናል። ይህን ማለታቸው ጥሩ። ምንም ተቃውሞ የለኝም ።
አንድ ኢትዮጵያዊ የፈለገውን የመከተል እና የማመን ጉዳይ ነው ። ሌላም ሌላም ይጨምሩ ስለነሱ ማውራት ሳይሆን ለኛም እድል ስጡን እኛም ስለ ኢትዮጵያ የምነለው ነገር አለ ስለ ወያኔም የምንነቅፈው ነገር አለን ይህ ነው ቁምነገሩ ፍርድ እና ውሳኔውን ለሕዝብ በመተው ሕዝብ የመረጠውን እንዲመራው ማድረግ ግድ ይላል።
ወያኔ ኢትዮጵያን ማስተዳደር ከጀመረ የማይታወቁና የማይፈለጉ ሃሳቦች እና ነገሮች ገብተዋል። ያም ህዝብ ወዶ ሳይሆን በግድ የህዝብ ሃሳብ ተጥሶ የአንድ የፖለቲካ ፓርቲ ሃሳብ እና አላማ እየተንጸባረቀ ነው። ባንዲራው ላይ ከተለጠፈችው ኮከብ ብንጀምር ከ90%
በላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ይህንን የኮከብ ምልእክት አርማ ያለውን ባንድራ አይቀበለውም ።የኮከቡ ትርጋሜውም ወይም አላማው ሌላ ነው። ኮከባ የምትገልጸው የስይጣንን አምላኪወችን ሲሆን በኢትዮጵያ ባንዲራ ላይ የተለጠፈው ኮከብ ሶስት ትረጔሜ አለው እነሱም እንደሚከተሉት ናቸው።
1 የኢትዮጵያን ህዝብ በሰይጣናዊ ሃይል ለማፍዘዝ ፦
2 ስይጣን ፍቅር ስለማያውቅ መለያየት እና መጣላት በኢትዮጵያ ህዝብ ውስጥ ለማስረጽ፦
3 የኢትዮጵያ ህዝብ አውቆም ሆነ ሳያውቅ የሰይጣን ምልክት የሆነውን የሰይጣንን ምልክት እንዲያውቅ እና ክፋታዊ የሰይጣንን አሰራር እንዲለማመድ ለማድረግ ነው።
በዚህ ዙርያ ትንሽ ብዬ ወደ ወያኔ ወደሆነችው አርማ እሄዳለው
በኢትዮጵያ ውስጥ ወያኔ ከገባ ጀምሮ የአገሬ ህዝብ ውስጥ ብዙ ክፋት አብሮ ገብቱአል። ለዚህም ኮከባ የወለደችው ወይም ያፈራችው ፍሬ ስናይ ከመቼውም ጊዜ በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ፍቅር ጠፍታል ። የኢትዮጵያ ህዝብም ብርን እና ጥቅምን አምላኪ ከመሆኑ የተነሳ ወንድም ወንድሙን ፤እህት እህቷን፤ ወላጆች ልጆቻቸውን ፤አሳልፈው ይስጣሉ። ሁሉም ስልጣን ናፋቂወች ሆነዋል። አባት ከልጁ፤ እህት ከወንድም፤ ዘር ከዘር ፤ጎሳ ከጎሳ ፤ሃይማኖት ከሃይማኖት፤ ኢትዮ ጵያ ውስጥ ከእለት ወደ እለት ግጭቶ ች እየተበራቱ ጥላቻወች በሰፊው እየታዩ ነው። እናት ሌባ ልጅ ቀማኘ የሚለው ቢሄል (አባባል) በአሁን በዘመነ ወያኔ እያየነው ነው። መሪዎች ተብዬዎች ሌባ ሎሌዎች ደግሞ ቀማኞች የሆነች ሐገር ከመሰለች ሰነባብታልብ ።የጠፋው ፍቅር እንዲመለስ እና የተወሰድብን ክብር እንዲመጣ የወያኔ አዚም የሆ ነችውን ኮ ከብ ከኢትዮጵያ ምድር ማጥፋት መቻል አለብን። ይህ ኮከብ ቢሄር ቤሄረስቦችን የሚወክል ሳይሆን ጥላቻና መለያየትን የሚያሰፍን ፍቅርን የሚያጠፋ የሰይጣንን ስረአት የመከተል እና የሠይጣንን አርማ ከፍ አድርጎ የማሳየት ስራ ነው።
ወደ ንብ ስንመጣ ደሞ ንብን ምረጡ... ንብን ምረጡ ...እያሉ መለፍለፍ ከጀመሩ ሰንብተዋል መረዟን ብቻ እንጂ ማሯን የማናየውን ንብን ፤በየአገሩ እየዞረች እሾኴን የምታራግፈዋን ንቧን፤ ማሯን ለንጉሶቻ ብቻ የምታበላዋን ንቧን ፤ህብረተሰባን ማሯን ታበላን ይሆን ብሎ የሚጠብቃት ተስፈኘዋን ንቧን ፤ይችን ንብ ነው ምረጡ የሚሉን።
የንብ በሀሪ የአንድ ቀፎ ንብ ከሌላ ቀፎ ንብ ጋር በፍጹም አይሰማማም ተሳስታ አንዷ ንብ ወደሌላ ቀፎ ከሄደች ይገድሏታል። ወያኔም ልክ የንብ በሀሪ ነው ያለው። ከወያኔወች ድርጅት ውጪ የሌላ ድርጅት የሆነ ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲኖር አይፈለግም ።
ንቦች ማራችውን የሚሰሩት ለራሳችው እና ለንጉሳ ቸው ብቻ ነው። ወያኔዎችም የሚሰሩት ለራሳችው እና ለሹማምቶቻችው ብቻ ነው።
ንቦች ለማር መስሪያ እንዲሁም ለቀፎ አገልግሎት የሚሆነውን በሙሉ የሚጠቀሙት ክቀፎአቸው ወጥተው በሰአት 100 ኪ. ሜ ያህል
በመብረር ከአካባቢያችው ስብሰበው ወደቀፎአቸው የገባሉ። ወያኔዎቸም የኢትዮጵያን ንብረት በሙሉ በሁሉም አቅጣጫ በመዘዋወር እየዘረፉ ለራሳቸው ያክማቻሉ። ንቦች የራሳቸው ባልሆነ ነገር ማራቸውን እየሰሩ የሌላ ቀፎ ንብ ግን ወደነሱ ቀፎ እንድትገባ አይፈልጉም ወያኔም ምንም ቅሬታ በሌላችው ስዎች የሌላውን ህብረተሰብ ሃብት ለመጠቀም ይስበሰባሉ። ሊላው ህብረተሰብ ወደ እነሱ ሲጠጋ ግን ያጠፉታል ።ስለዚህ የንብን ማር መብላት የሚችለው የቀፎወቹ ንቦች ብቻ ናቸው። የኢትዮጵያንን ሃብት እየበላ እና እየተጠቀመ ያለው ብቻውን ወያኔ ነው።
ኢትዮጵያ ማር ነች ማርን ደግሞ ሁሉም ይፈልጉታል አንድም ለመብላት አንድም ለመድሃኒት። ማር መብላት ካማሮት ወደ ንብ ቀፎ ባዶ እጅ አይኬድም እንደጭስ ያለ መከላከያ እና ማሩን መቁረጫ ቢላ ያስፈልጋል። ካለበለዝያ ግን በመርዝ ተወግተው ይሞታሉ። ወያኔም እንደዚሁ ነው የኢትዮጵያን ሃብትና ንብረትን የብቻው አድርጎ ማስተዳደር ከጀመረ ሰንብታል ስለዚህ ኢትዮጵያ የምትባለው አገር የወያኔ ብቻ መስሎ ከታያቸው ሰንብታል። የኢትዮጵያ ሃብት የኢትዮጵያን እንጂ የጥቂቶች ብቻ አይደለችም ብሎ ለመጠቀም እና ለሁሉም ለማዳረስ ባዶ እጅ ተኪዶ አይሆንም ።በባዶ እጅ ከተኬደ በመረዛቸው ወግተው ስለሚገሉ መከላከያ አድርገን ኢትዮ ጵያን ማዳን ግድ ይለናል። ስለዚህም ምርጫ ..ምርጫ.... የሚለው የወያኔ የማደናገርያ ዘዴ ነው እና ይህ ምርጫ አልጫ እንደሆነ እና ትርጉም የሌለው መሆኑን ልንረዳው ይገባል። አልጫ የሆነው ምርጫ የሚለወጠው አልያም የጣፈጠ የሚሆነው የሁሉም ኢትዮጵያዊ የነቃ ተሳትፎ ሲያደርግ ነው። ንብን በማጥፋት በመርዙ ከመወጋት እና ከመሞት የኢትዮጵያ ሕዝቡ ነጻ ሁኑ። ባንዲራው ላይ ያለችውን ኮከብ በማስወገድ የሰይጣንን መንፈስ የኢትዮጵያ አርማ ከመሆን እንከላከል እላለው።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !!!!!!
ከ አዲስ ብርሃኑ
Email.. berhanu.addis@yahoo.com
Friday, 15 May 2015
በፍርሃት ውስጥ ያለው የኢሕአዴግ ሥርዓት የማዕከላዊ ዕዝ ወታደሮች ከቦታ ቦታ እንዳይንቀሳቀሱ ጥብቅ መመሪያ አወረደ!
የኢህአዴግ ስርአት የማእከላዊ እዝ ወታደሮች ከቦታ ወደ ቦታ እንዳይንቀሳቀሱ ጥብቅ መምሪያ እንዳወረዱላቸው ምንጮቻችን ገለፁ ሲል የደህሚት ድምጽ ዘገበ:: በአዲ-ኮኮብ የሰፈሩት የማእከላዊ እዝ የበታች አመራር ወታደሮችና ተራ ወታደሮች ከአካባቢው ህብረተሰብ ጋር እንዳይገናኙና ወደ አዲ-ዳዕሮና ሸራሮ እንዳይንቀሳቀሱ ተከልክለው እንደሚገኙ የገለጸው የደህሚት ድምጽ እነዚህ የበላይ አመራሮች ሰራዊቱን በመሰብሰብ በአዲ-ዳዕሮ፤ አዲ ነብሪ ኢድ፤ አዲ-ሃገራይ፤ ሸራሮና አካባቢው በአጠቃላይ በአካባቢው የሚገኝ ህብረተሰብ የትህዴን አባል ሰለሆነ የምናጣራው ነገር አለን መንቀሳቀስ ክልክል ነው በማለት ትእዛዝ እንዳወረዱላቸው ለማወቅ ተችሏል። በተጨምሪም- ወታደሮቹ በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ ጥላቻ እንዲያሳድሩና ከሱ ጋር እንዳይወግኑ የሃሰት ፕሮፖጋንዳ ቅስቀሳ ሲሰጥ የሰነበተ ሲሆን ስርአቱ ከህዝብ ተነጥሎ በጠምንጃ ሃይል ብቻ የቆመ እንደሆነ በሚገባ ሰለሚያውቅ ወታደሮቹ ደግሞ ስርአቱን በመተው ከህዝባቸው ጋር እንዳይወግኑ በመስጋት የመነጨ መሆኑን ወታደሮቹ በሚገባ እንደተረዱት ለመረጃ ምንጩ የደረሰው መረጃ አስረድቷል።
Thursday, 7 May 2015
የቁልቁለቱን ጉዞ እናስቁም፤ ውርደት ይብቃን!!!
የህወሓት አገዛዝ ፋሽስታዊ ባህርያት እያደር መረን እያጣ፤ ነውረኛ እየሆነ መጥቷል። በአሳለፍነው ሣምንት ብቻ እንኳን አስነዋሪ ይዘት ያላቸው ሁለት ፋሽስታዊ ክስተቶችን አስተውለናል።
አንዱ በምርመራ ስም በታሳሪዎች ላይ የሚደረገው አሳፋሪ ሰቆቃ ነው። በገላቸው በሚያፌዙና በሚሳለቁ ተቃራኒ ፆታ መርማሪዎች ፊት ለሰዓታት ተመርማሪዎች ራቁታቸውን እንዲሆኑ የሚደረግበት እና እየተፌዘባቸው የሚደበደቡበት ሥርዓት መኖሩ የጉዳቱ ሰለባዎች ይፋ ሲያወጡ እፍረቱ ለመርማሪዎቹ ብቻ ሳይሆን ይህንን ጉድ ተሸክመን ለኖርነው ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ነው። በተለይም ደግሞ እንዲህ ዓይነት ክብረነክ ሰቆቃ በሴቶች ላይ እየተፈፀመ መሆኑን ስንሰማ አገራዊ ውርደቱ ያሸማቅቀናል። እንዲህ ዓይነቶችን በሰው ስቃይና እፍረት የሚዝናኑ ጉዶችን ተሸክመን የምኖር መሆናችን ሁላችንን ያዋርደናል። ይህንን አስነዋሪ “የምርመራ ዘዴ” ያጋለጡት የዞን 9 ብሎገሮች፣ ጋዜጠኞችና ፓለቲከኞች ክብርና ሞገስ የሚገባቸው ጀግኖች ሲሆኑ የተዋረዱት እነሱ ሳይሆኑ እኛ ኢትዮጵያዊያን መሆናችን ሊሰማንና “ውርደት በቃ” ልንል ይገባናል።
ሁለተኛው አሳፋሪ ድርጊት ደግሞ ወገኖቻችንን በግፍ ባረደው አይሲስ በተሰኘው አሸባሪ ድርጅት ላይ የህወሓት አገዛዝ የተለሳለሰ አቋም ወስዷል ብለው ራሱ ህወሓት በጠራው ሰልፍ ላይ ተቃውሞዓቸውን ባሰሙ ወጣቶች ላይ አገዛዙ የወሰደው የኃይል እርምጃና ከዚያም ወዲህ እየተደረገ ያለው ነገር ነው። አገዛዙ ለፕሮፖጋንዳው ይጠቅመኛል ብሎ በጠራው ሰልፍ ወጥተው ተቃውሞዓቸውን የገለፁ ወጣቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተደብድበዋል፤ በጅምላ ወደ እስር ቤቶች ተግዘዋል። የአገዛዙ ካድሬዎች ወገኖቻችንን የፈጀውን አይሲስን በመቃወም ፋንታ የራሱ የህወሓትን ውል አልባ ህግ አክብረው በመንቀሳቀስ ላይ ያሉትን ሰማያዊ ፓርቲ፣ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን እና አረና ፓርቲን እየወነጀሉ መሆኑ አጅግ አሳፋሪ ነገር ነው። የአይሲስን አረመኔአዊ ድርጊት ከኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጋር ለማገናኘት በህወሓት የደህንነት ቢሮ አማካይነት እንቅስቃሴ መጀመሩ እየተሰማ ነው። ለወጣቱ በብዛት መሰደድ በምክንያትነት የሚያቀርቡት ደላሎችን መሆኑ አላዋቂነት ሳይሆን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ቅራኔው በኢትዮጵያዊያን መካከል እርስ በርስ እንዲሆን ያለመ መሠሪነት ነው። ከዚህም አልፎ የትግራይ ወጣቶችን ነጥሎ በመሰብሰብ “ትምክህተኞች ሊበሉህ ነውና ታጥቀህ ሳይቀድሙህ ቅደም” እያሉ መቀስቀስ በመንግሥት ደረጃ የእርስ በርስ እልቂትን ከማደራጀት ተለይቶ አይታይም። የሥርዓቱ ይሉኝታ ቢስነት የደረሰበት ዝቅጠት ገላጭ ከሆኑ ነገሮች አንዱ “እስከምርጫ መጨረሻ ድረስ ልጆቻችሁን አስረን እናቆይላችሁ” እያሉ ወላጆችን እስከመጠየቅ መድፈራቸው ነው።
ከላይ በአጭሩ የተዘረዘሩት ኩነቶች የሚያረጋግጡት ህወሓት የተማከለ አመራር አጥተው መንገድ የጠፋቸው፤ ሆኖም ግን እጃቸው ውስጥ የገባው ስልጣንና ሀብት ላለማጣት ምንም ነገር ከማድረግ የማይመለሱ አውሬዎች ስብስብ መሆኑ ነው። እንዲህ ዓይነቱን የአውሬዎች ስብስብ የሚገዛው የህግም ሆነ የሥነ-ምግባር ገደብ የለም። ህወሓት እስር በርሳችንን አባልቶ አገራችንንና ሕዝቧን ወደ ማንወጣው አዘቅት ከመክተቱ በፊት ራሱ ህወሓትን ማስወገድ እና በምትኩት ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን መገንባት የዚህ ትውልድ ኃላፊነት ነው። ይህ ካላደረግን አሁን በወህኒ ቤቶች የሚደረገው ዜጎችን ልብስን አስወልቆ የማዋረድ አስነዋሪ ተግባር ነገ በአደባባዮች የማይደረግ ስለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ የለንም። ይህ ትውልድ ኃላፊነቱ ካልተወጣ ህግን አክብረው ከአገዛዙ የተለየ ሀሳብ እናራምዳለን የሚሉ ወገኖቻችን በሙሉ አደጋ ውስጥ ናቸው። በህወሓት መሠሪ ተግባራት ሳቢያ በክርስትናና እስልምና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያን መካከል ያለው መግባባት እንዲሻክር እየተደረገ ነው። ዜጎችን በማዋረድ የሚደሰት አገዛዝና ለመዋረድ የፈቀደ ሕዝብ እስካለ ድረስ የቁልቁለቱ ጉዞ መጨረሻ የለውም። ይህንን ማስቆም ያለብን እኛ ሁላንችንም ነን። በአደባባይ መደራጀት ሲከለከል በምስጢር መደራጀትን መልመድ የኛ ኃላፊነት ነው። የኢትዮጵያ አርበኞች ድል መታሰቢያ በዓልን ስናከብር ከቀደምቶቻችን ልንወርስ ከሚገቡን እሴቶች አንዱ ለክብራችን ዋጋ መክፈል ያለብን መሆኑን ጭምር ነው። የኢትዮጵያዊያን ክብር በወያኔ ሲዋረድ እያየን ዝምታን ከመረጥን ከዚህም የባሰ እንዲመጣ መፍቀዳችንን እንወቀው።
አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የዜጎችና የአገር ውርደት ይብቃ! በተባበረ ክንድ ህወሓት ይወገድ፤ በምትኩም ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመመሥረት መሠረት እንጣል፤ ይህንን ታላቅ ኃላፊነት ለመወጣት በኅብረት እንነሳ ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!
Source www.patriotg7.org
Monday, 6 April 2015
ወቅቱ የተግባራዊ ትግል ነው!
ለገዛ ራሱ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ እና ለኢትዮጵያ ቅን የሚመኝ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ህወሓትን ለማስወገድ ተግባራዊ ትግል ውስጥ መሳተፍ የሚኖርበት ወቅት ላይ እንገኛለን። በዚህ ወሳኝ ወቅት ከዳር ሆኖ መታዘብ ዘረኛውን፣ አምባገነኑን፣ ፋሽስቱን ህወሓት እንደመደገፍ ይቆጠራል።
ዛሬ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ህሊናውና አቅሙ በሚፈቅድለት የትግል ዘርፍ የመሰማራት ሰፊ እድል ተፈጥሮለታል። በዚህም መሠረት የህወሓትን አፈና በጠነከረ ክንድ ለመመከት የቆረጡ ኢትዮጵያዊያን ወደ በረሃዎችና ተራራዎች አቅንተዋል። ብዙዎች በመንገዱ ላይ ያሉ ጋሬጣዎችን ተቋቁመው እየተቀላቀሏቸው ነው። በደል የመረራቸው ሌሎች በርካታ ኢትዮጵያዊያን በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በቡድን ለነፃነታቸው ዘብ ቆመው በህወሓትና አገልጋዮቹ ላይ እርምጃ መውሰድ ጀምረዋል። ይህ የሚበረታታ እና ተቀናጅቶ ሊጠናከር የሚገባው ጉዳይ ነው።
አሁን ያለንበት ጊዜ ልዩ የትግል ወቅት ነው። ትናንት በከተሞች ይካሄድ የነበረው ፀረ ወያኔ ትግል ዓይነተኛ መታወቂያው ሕዝባዊ ተቃውሞ ነበር። ዛሬ ግን ይህ ሁኔታ ተቀይሯል። በተለይ በአገዛዙ ፈቃድ የሚደረጉ ተቃውሞዎች ፋይዳ ቢስ ሆነዋል። በአገዛዙ ፈቃድ በሚደረጉ ተቃውሞዎች ለውጥ እንደማይመጣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በማያሻማ ሁኔታ ተረድቷል። ስለሆነም ትግሉ ወደ ሕዝባዊ እምቢተኝነት አድጓል።
ዛሬ ከዚህ በፊት ያልተሞከሩ የትግል ስልቶች ተግባራዊ እየሆኑ ነው። በዚህ ረገድ የሙስሊም ኢትዮጵያዊያን የተቀናጁ ርምጃዎች በአርዓያነት የሚጠቀሱና የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ድጋፍ የሚሹ ናቸው። እነዚህ የሕዝባዊ እምቢተኝነት ተግባራት የእምነት አጥር ሳይለያየን ፍትህ የተጠማን ዜጎች ሁሉ ልንተገብራቸው የሚገቡ ናቸው።
ለምሳሌ፣ ተንቀሳቃሽ ስልኮችን በተወሰኑ ቀናት መዝጋት በተቀናጀ ሁኔታ ከተደረገ ከፍተኛ ውጤት ሊያመጣ የሚችል፤ በሙስሊም ወገኖቻችን ግንባር ቀደም መሪነትና አስተባባሪነት ተሞክሮ በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል መሆኑ የታየ አንድ የትግል ስልት ነው።
በአሁኑ ወቅት ተግባራዊ በመደረግ ላይ ያለው ሣንቲሞችን የመሰብሰብ ዘመቻም ሌላ ከዚህ በፊት ያልተሞከረ፤ በተጨማሪ እርምጃዎች ከታገዘ ህወሓት መራሹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን ገንዘብ መቆጣጠር የማይችልበት ደረጃ ላይ ሊያደርስ የሚችል ጉልበት ያለው ስልት ነው። ውሳኔው ሣንቲሞችን ብቻ ሳይሆን የወረቀት ኖቶችንም ሲያካትት በዝውውር ላይ የሚኖረውን ገንዘብ ብዛት የሚቆጣጠረው ህወሓት ሳይሆን በደል ያንገሸገሸው ሕዝብ ይሆናል። በባንኮች ያለ ተቀማጭ ገንዘብ በማውጣትም የህወሓት የፋይናንስ ተቋማትን ማሽመድመድ ሌላ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል ስልት ነው። በእነዚህ እርምጃዎች የተለማመደ ሕዝብም ወደ ግዢ እቀባ፤ ለተወሰኑ ቀናት ከቤት አለመውጣት ብሎም “ግብር አልከፍልም” ወደማለት ሊሸጋገር ይችላል።
እንዲህ ዓይነቱ ስልቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ግን የመላው ሕዝብ ተሳትፎ እና የተቀናጀ አሠራርን ይፈልጋል። ለምሳሌ፣ ሰብስቡ ሲባል መሰብሰብን፤ በትኑ ሲባል መበተን ይጠይቃል። እንዲህ ዓይነት የተቀናጁ የጋራ እርምጃዎች በአምባገኑ የህወሓት አገዛዝ ላይ ከሚያደርሱት ጥቃት በተጨማሪ በኢትዮጵያዊያን መካከል ያለውን መግባባት ያጠናክራሉ። እንዲህ ዓይነት የተቀናጁ የጋራ እርምጃዎች በማኅበረሰብ ቡድኖች መካከል አዎንታዊ መስተጋብር ለመፍጠር የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ ነው።
አሁን አገራችን የምትገኝበት ሁኔታ በጥሞና ሲጤን የኢትዮጵያ ሕዝብ ሳይነጋገር መግባባት፣ እርስ በርሱ መናበብ የሚችልበት ደረጃ ላይ እየደረሰ መሆኑ መረዳት ይቻላል። ይህ ስነልቦናዊ ዝግጅት ደረጃ በደረጃ ጠንከር ያሉ እርምጃዎችን ለመውሰድ ያዘጋጀናል።
በማናቸውም የጋራ እርምጃዎች ለግል ጥቅሞቻቸው ቅድሚያ የሚሰጡ፤ ራሳቸው “ብልጥ” አድርገው በማየት በተፈጠረው ሁኔታ መጠቀም የሚፈልጉ፤ በሌላው ድካም ለማትረፍ የሚሯሯጡ ሰዎች መኖራቸው የማይቀር ነው። ህወሓት ለሃያ አራት ዓመታት ኮትኩቶ ያሳደገው የአድርባይነት ባህልም ሌላው እንቅፋት ሊሆን እንደሚችል መገመት ቀላል ነው። ድህነት ደግሞ በገዢዎች ላይ ጨክነን የመነሳት አቅማችንን እንደሚያዳክም የታወቀ ነው። ሆኖም ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከፊቱ የቀረበለት ምርጫ “ባርነት ወይስ ነፃነት” መሆኑን የተገነዘበበት ጊዜ ላይ ደርሰናል።
በዚህም ምክንያት ለህወሓት ባርነት ከመገዛት ነፃነትን የሚመርጥ ዜጋ ሁሉ ዋጋ ለመክፈል መዘጋጀት ይኖርበታል። ለሁላችንም የሚሆን የትግል ዘርፍ መኖሩ የሕዝቡን ተሳትፎ ከፍ ያደርገዋል። የሁለገብ ትግል ስትራቴጂ ጥቅሙም እዚህ ላይ ነው። ማንም የማንም ነፃ አውጭ አይደለም። ሁላችንም ተባብረን ሁላችንንም ነፃ እናወጣለን።
አርበኖች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ “ትግላችን ዘርፈ ብዙ ነው፤ ተግባራዊ ትግል የሚደረገውን በሁሉም ቦታዎች ነው፤ እርጃዎቻችን እናቀናጅ፤ ወቅቱ የተግባራዊ ትግል ነው” ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!
Friday, 27 March 2015
የኛ የኢትዮጵያውያን ጥያቄ ስር ነቀል አብዮታዊ ለውጥ ጥያቄ ነው
ኢትዮጵያውያን ለነጻነታችን ዋጋ መክፈል የጀመርነው ከጥንት ጀምሮ መሆኑ ይታወቃል:: በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ተንሰራፍቶየሚገኘው የዘረኛውና ቡድናዊው አገዛዝ በዜጎች ላይ ከፍተኛ በደል በማድረስ ላይ ይገኛል:: ከዚህ ጨቋኝ አገዛዝ ለመገላገልበአንድነትና በመተባበር ለነጻነታችን መታገል አለብን:: ላለፉት 24 አመታት በኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ የተቀመጠውንዘራፊውን እና ጨቋኙን የወያኔ ጁንታን ለመቅበር የአንድነት እና የለውጥ ሃይሎች ልዩነቶቻችንን በማቻቻል በጋራ ልንታገልየሚገባና ለውጥ ልናመጣ የሚገባ ችላ የማይባል ዋነኛ ጉዳይ ነው። በህዝባችን ላይ ከፍተኛ እንግልት፣ እስር፣ ሰቆቃ፣ ግድያወዘተ እየፈጸመ የሚገኘው የህዝባችንና የሃገራችን ጠላት ወያኔ እና ወያኔ ብቻ ነው::
ባሳለፍናቸው መራር የትግል አመታት ውስጥ በቅርቡ እንዳየነው የተቃዋሚዎች በመዋሃድና አንድነትን ከመፍጠር ይልቅ እርስበእርስ መፈራረጅና መወነጃጀል ለስልጣን መሮጥ እንዲሁም ለስም እና ለዝና መትጋት ነው:: ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተረፈው ነገርቢኖር ከጭቆና ወደ ባሰ ጭቆና ማቅ ውስጥ ከመዘፈቅ ውጪ ፍጹም የናፈቀውን የነጻነት አየር እንዲተነፍስ አላደረግነውም።የተቃዋሚ ሃይሎች ጥንካሬ እንዲጎለብት በየድርጅቱ ውስጥ ያሉትን እንከኖች በማጥራት በጋራ እና በተመቻቸ የሃሳብ መግባባትተቻችሎ እና ተግባብቶ የትግል ስትራቴጂን ከግብ ለማድረስ ህብረ-ብሄር የሆኑት የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር እና ግንቦት7 እንዳደረጉት ለአንድነትና ለትብብር ተግቶ መስራት ይጠበቅብናል። በአሁኑ ወቅት ይህንን ዘረኛ ስርዓት ለማውረድ በውስጥምሆነ በውጭም ትግሉ በስፋት ቀጥሎ ይገኛል:: ወያኔ እስኪወድቅና ህዝባችን ድል እስኪቀዳጅ ድረስ ሊቀጥል የሚገባው ትግልእንደመሆኑ መጠን ከበፊቱ በተሻለ ሁኔታ የተያዘው ትግል በአሁኑ ሰአት ወያኔን እያፍረከረከ በፍርሃት እንዲሸበር አድርጎታል::
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥ ይፈልጋል! የኛ የኢትዮጵያውያን ጥያቄ አብዮታዊ የለውጥ ጥያቄ ነው። የፖለቲካ አስተዳደር ለውጥ ፣የኑሮ ውድነት የሚያላቅቅ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ለውጥ፣ በጋራ ህብረተሰባዊነትና እኩልነት ላይ የተመሰረተ አገዛዝ ወይንም መንግስትእንደምናገኝ የሚያረጋግጥልን ለውጥ እንፈልጋለን፡፡ የማህበራዊና ፍትህ እኩልነት ለውጥ፣ የነጻነት እና የመብት ማግኘት ጥያቄ፣ከመንግስት ነጻ የሆነ ፍርድ ቤት፣ በሃገራችን ተዘዋውረን በፈለግነው ቦታ የመስራት እና የመኖር ጥያቄ የሚያረጋግጥልን ለውጥእንፈልጋለን፡፡ በሃገራችን ላይ የሃገራችን ባለቤቶች ስንሆን የሚገኘው ብልጽግና እና እድገት ባለቤት መሆናችንን የሚያረጋግጥልንለውጥ እንፈልጋለን፡፡ ይህ ሳይታለም የተፈታ እና የሁሉም የነጻነት ፈላጊ ሃይሎች ጥያቄ ነው። ሰብአዊ መብቶች ለዲሞክሪያሲያዊስርአት ግንባታና ለአንድ ሀገር ልማትና ብልፅግና መሰረታዊ ነገሮች ተደርገው የሚወሰዱ ናቸው፡፡ ዜጎች የሃገራቸው ሃብትባለቤትና የመጠቀምም መብት እንዲሁም ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብት ሊኖረን ይገባል::
በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉትን ፓርቲዎች መዋቅሮቻቸውን በማጠናከር የውስጥ ድክመቶቻቸውንም በመቅረፍእንዲጠነክሩ የማድረግ ግዴታ ከሁላችንም ከለውጥ ፈላጊ ሃይሎች ይጠበቃል።ሙሉውን ለማንበብ ይህን ይጫኑ
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
Sunday, 15 March 2015
ሰማያዊ ፓርቲ ቅስቀሳ እንዳያደርግ እንቅፋት እየተፈጠረበት ነው
ሰማያዊ ፓርቲ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ቅስቀሳ እንዳያደርግ በፖሊሶች ክልከላና ወከባ እየደረሰበት እንደሚገኝ የሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ጉዳይ ኃላፊና ም/ሊቀመንበሩ አቶ ስለሽ ፈይሳ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ዛሬ መጋቢት 5/2007 ዓ.ም ፓርቲው በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ቅስቀሳ ያደረገ ሲሆን በባህርዳርና ወላይታ ዞን ፖሊስ የተለያዩ ምክንያቶችን በመፍጠር ቅስቀሰውን ማደናቀፉን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡
ዛሬ ሰማያዊ ፓርቲ በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ ቅስቀሳ በሚያደርግበት ወቅት የከተማው ፖሊስ ‹‹የምርጫ ቅስቀሳ አልተጀመረም›› ብሎ ያዋከበ ሲሆን የፓርቲው አመራሮችና አባላት ቅስቀሳ መጀመሩን ገልጸው ስራቸውን እያከናወኑ በነበሩበት ወቅት ‹‹ህገ ወጥ ሰላማዊ ሰልፍ›› አድርጋችኋል በሚል ሌላ ክስ 8 የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎችንና ሌሎች አባላትን በማሰር ቅስቀሳውን እንዳደናቀፈ የወላይታ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ታደመ ፈቃዱ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
በተመሳሳይ በባህርዳር ከተማ ፖሊስ ‹‹በሞንታርቮ ለመቀስቀስ ፈቃድ ስላላመጣችሁ መቀስቀስ አትችሉም፡፡›› በሚል ፓርቲው ሊያደርገው የነበረውን የምርጫ ቅስቀሳ እንዳደናቀፈ የፓርቲው የምዕራብ ጎጃም ዞን ጊዜያዊ አስተባባሪ አቶ አዲሱ ጌታነህ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ‹ለምን ትከለክሏቸዋላችሁ?› በሚል ህዝቡ ፖሊሶቹን በማፋጠጡ በድምፅ መቀስቀስ ባንችልም በህዝቡ ድጋፍ የቅስቀሳ ወረቀቶችን በማሰራጨት የተሳካ ቅስቀሳ አድርገናል›› ሲሉ አቶ አዲሱ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
በዚህ ወቅት ቅስቀሳ ለማድረግ ምንም አይነት ፈቃድ እንደማያስፈልግ የገለፁት አቶ ስለሽ ፖሊስ የሚፈጥረው እንቅፋት ሆን ተብሎ ሰማያዊ ወደ ህዝብ እንዳይደርስ የተቀየሰ ስልት ነው ብለዋል፡፡ ኃላፊው አክለውም ‹‹የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎችን በመሰረዝ ፓርቲው ምርጫው ላይ የሚፈጥረውን ጫና ለመቀነስ ጥረዋል፡፡ ይህ አልበቃ ሲልም የቅስቀሳ መልዕክቶቻችን በተደጋጋሚ በሚዲያ እንዳይተላለፉ እያደረጉ ነው፡፡ አሁን ደግሞ ወደ ህዝብ እንዳንደርስ በህገ ወጥ መንገድ በፖሊስ ማስቆም ጀምረዋል›› ብለዋል፡፡
በሌላ ዜና የጅማ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ባልታወቁ ግለሰቦች መዘረፉን የምርጫ ጉዳይ ኃላፊው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹በ02/07/07 ሁለት ሰዓት ላይ አራት ግለሰቦች ጽ/ቤቱን በመስበርና የጽ/ቤቱን ጥበቃ አስፈራርተው በማባረር ለቅስቀሳ የተላከ 6 ሺህ ኦሮምኛ በራሪ ወረቀት እንዲሁም 3 ሺህ አማርኛ በራሪ ወረቀት፣ አንድ የፎቶ ካሜራ፣ አንድ ባነር፣ ለሸካ ዞን ሊላክ የተዘጋጀ 5 ሺህ በራሪ ወረቀት፣ 50 ፖስተር፣ አንድ የእጅ ሜጋ ፎን፣ ሁለት ባነር፣ በርካታ ጋዜጦችና መጽሔቶች ሲዘርፉ የጽ/ቤቱን ኮምፒውተርም ሰብረዋል›› ሲሉ ኃላፊው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡
Wednesday, 4 March 2015
በአገር ሙሉ ጀግና ሞልቶ ወያኔን ጀግና አሉት።
ሀገራችን የጀግና ደሀ አይደለችም ጀግኖች የሞሉባት ሀገር ናት። በየተሰለፍንበት መሰኩ አለምን ያስደመመ ጀግኖች ያፈራች አገር ነች።በትምህርቱ ዘርፍ እስከ ሳይንቲስት የደረሱ የትምህርት ጀግኖች አሉ። በሰዕሉ እስከ የአለም ሎሬት የደረሱ የስእል ባለሞያ ጀግኖች አሉን። በስፖርቱም እስከ ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሌያና የአለምን ክብረ ወሠን የሚሰብሩ ጀግኖች ልጆችን ያፈራች አገር ነች። በኪነ ጥበቡ ጥግ ድረስ የደረሱ የኪነ ጥበብ ጀግኖች አሉን። በምርምሩም አዳዲስ ፈጣሪዎችን የሚፈጥሩ ድንቅዬ እና ብርቅዬ ልጆች አሉን። መቼም ጀግና አጥተን የጀግና ደሀ ሆና አታዉቅም አገራችንን የሚያኮሩዋት ጀግኖች አሉዋት የጀግናም ጀግና። - ወያኔን ጀግና አሉት! በTPLF የትግል ድርሻ ያለው እና ታጋዮች ጭምር ተወዳጅ የሆነውን ታጋይ ኃየሎም አርአያ በትግል ግዜ ሁሌም ካጠገባቸዉ እንዳይለይ የሚፈልጉት በቆራጥነቱ እና በችሎታዉ ታጋዬች በሙሉ የሚተማመኑበት ሀየሎም አርአያ ቀድሞም የጀኔሪል ማእረግ የተሰጠዉ ሰራዊቱ በጣም ስለሚወደዉ አና ስለሚያከብረዉ የተሸበሩት የTPLF መሪ ተብዬዎች ነገ ትልቅ ቦታ እንደሚይዝ እና የወያኔዎችን ኃሳብ ሊቀበላቸዉ እንደማይችል ስለሚያቁ ያንን ከባድ ጊዜያቶችን አሳልፎ የመጣዉን ታጋይ እየተዝናና ባለበት ሰአት አንድ ተራ የወያኔ ካድሬ በበላዮቹ TPLF ሰዎች ትእዛዝ ተሰጥቶት ሳያስበዉ በመሳሪያ ተኩሶ በመምታት ገደለውታል። ይሄ ነዉ የወያኔ ጀግንነት?
በትግሉ ሰአት አብሮአቸዉ የነበሩት የትግራይ ሰዎች ትግሉንም በድል ያጠናቀቁትን የትግራይ ልጆች ከድል በኋላ ከወያኔ ጋር የሀሳብ ልዩነት በመኖራቸዉ ብቻ በድብቅ አየተከታተሉ ከሰላሳ ስድስት ሺህ በላይ ታጋዬችን የገደሉ እንግዲህ እዚህን ገዳዬች ነዉ ጀግኖች የምትሉት?
ሀዉዜን ላይ የወረደዉ የቦብ ዝናብ በደርግ ባለስልጣን ዉስጥ ሆኖ ትዕዛዝ ያስላለፈዉ አና ይህንን ምስኪን ሕዝብ ለድብቅ አላማቸዉ የሰዉ ሀይል ለማግኛ ተበዳይ ለመምሰል ወደ ሀዉዜን ገበያ የወያኔ ወታደር በሙሉ ገብተዋል ተብሎ እንዲነገር አስደርገዉ የትግራይን ሕዝብ ዳር ቆመው ያስፈጁትን ወያኔን ጀግና አሉት።
አዲስ አበባ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ በወጡ ምንም የጦር መሳሪያ ባልያዙ ንፁሀን ዜጎጀ ላይ የፈሪ ዱላ አንደሚባለው በያዙት መሳሪያ ያለምንም ርህራሄ ህዝቡን የፈጁት ነዉ እንግዲህ ጀግና የምትሉን?
ጋንቤላ ላይ ከመሬታችን አታፈናቅሉን በመሬታችን መኖር እንፈልጋለን ብለዉ መሬታችንን ለባዕዳን አትስጡብን ብለዉ ተቃዉሞ ባሰሙት ንፁሁን የጋቤላ ተወላጆች ላይ ብረት አንስግቶ የፈጀዉና በግዳጅ ከመሬታቸዉ አፈናቅሎ ለባድ የሚሰጠዉን ነው ዉያኔን ጀግና የምትሉት?
በአኝዋከ ህዝብ ላይ መሬታቸዉን በመፈለግ የአኝዋከ ህብረተሰብን ዘግናኝ በሆነ መልኩ የዘር ማጥፋት እልቂት ከደረሰ በኋላ በጅምላ ወደ አንድ ጉድጓድ የከተተዉን ነዉ ጀግና ብላቹ የምትጠሩት?
በኦጋዴን ዉሰ በሱማሌ ተወላጆች ህብረተሰብ ላይ በአየር ቦምብ በማዝነብ የዘር ማጥፋት የፈፀመዉን እና እንደ ሃውዜን ውስጥ እንዳደረጉት ጭካኔ የተሞላበት ስራቸውን የደገሙትን ነዉ ጀግና ያላችኋተው?
አንቦ ላይ በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን መሰረት ተቃዉሞ የወጣዉን የአምቦ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ላይ የታጠቀ ወታደር አሰማርቶ ተማሪዎችን መግደል ነዉ እንዴ ወያኔን ጀግና ያሰኘዉ?
ባህር ዳር ላይ ስለሀይማኖት ብለዉ የወጡት ሰላማዊ ሕዝብ ላይ አነጣጥሮ ተኩሶ መግደል ነዉ ጀግና ያሰኛቸዉ ታድያ ጀግና ያሰኛቸዉ ምንድን ነዉ?
ብዕር የያዘ ጋዜጠኛ አንተ አሸባሪ ነህ ብሎ ወደ እስር መጣል ነዉ ጀግንነት? ወይስ የፖለቲካ ሰዎችን ባላቸዉ የፖለቲካ አቋም በመፍራት ብቻ የአሸባሪ ታፔላ እየለጠፉ ወደ ወይኒ መወርወር ነዉ ጀግንነት? ወይስ የተማረዉንም ያልተማረዉንም ሰዉ በኛ መስመር ግባ ካልገባህ መኖር አትችልም ብለዉ ማዋከብ ነዉ ጀግና ያሰኛቸዉ?
ጀግና ማለት በፍቅር ታግሎ በፍቅር የሚያሸንፍ ነዉ። ጀግና ማለት ከባርነት ቀንበር አላቆ ነፃነትን የሚያወርስ እና በነፃነት እንዲኖሩ ማድረግ ነዉ።ጀግና ማለት ስራዉ ከሚናገዉ በበጠ ጏልቶ የሚታይ እና በሰዉም ዘንድ ተቀይነትን ያገኘ ነዉ።
ጀግና ማለት እንደ ዉሻ ላበላዉ የሚጮህ ሳይሆን ለእዉነት የቆመ ለእዉነት የተሸነፈ ለእዉነት የሚኖር እሱ ነዉ ጀግና። መሳርያ ስለያዘ ብቻ ከኔ በላይ ማን አለብኝ ብሎ እየተኯሰ ሰላማዊ ሰዉን የሚገል እሱ ጀግና ሳይሆን አረመኔ ነዉ አረመኔን ደሞ ጀግኖች ያጠፉታል።
ጀግና ማለት ለነሱ የታጠቀ ኃይል በሰላማዊ ሰዉ ላይ ተኩሶ መግደል ከመሰላቸዉ፡ ጀግና ማለት ለነሱ ብዕር የያዙትን ብዕራዉያንን በብረት አስረዉ ማሰቃየት ከሆነ፡ ጀግና ማለት ለነሱ የፓለቲካ ሰዎችን በአአስከፊ ቅጣት መቅጣት ከመሠላው፡ እኔ ግን እላለዉ እነዚህ ጀግና ሳይሆኑ ፈሪ እና እውቀት የጏደላቸዉ ናቸዉ። እነዚህ ጀግና ሳይሆኑ የጨነቃቸዉ ናቸዉ እላለዉ። ፈሪና የጨነቀዉ ሰዉ የሚያደርገዉን ድርጊት እያደረጉት ያሉት።
ጀግናማ ፍቅርን አስተማሪ ነዉ። ጀግናማ ለህዝብ የቆመ ነዉ። ጀግናማ ለሆዱ ያልቆመ ነዉ። ጀግናማ ኢትዮጵያዊው ነው።
To Addis Berhanu
03.03.2015
Email- berhanu.addis@yahoo.com
- See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/5049#sthash.m7pSsFra.dpuf
Subscribe to:
Posts (Atom)






