Friday, 24 October 2014
የህዝብ ግንኙነት ካድሬዎች በማህበራዊ ድረ ገጾች ላይ ሊዘምቱ ነው
ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአቶ ሬድዋን ሁሴን የሚመራው የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት አሰልጥኖ በፌዴራል የመንግስት ተቋማት በህዝብ ግንኙነት ኃላፊነት ለመደባቸው ካድሬዎች የሁለት ቀናት የማህበራዊ ድረገጾች አጠቃቀም ስልጠና በመስጠት በተለይ በግንቦት ወር ከሚካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ እንዲሳካ የበኩላቸውን አዎንታዊ ሚና እንዲጫወቱ አደራ ተጥሎባቸዋል፡፡
የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን እንደገለጸው የኮምኒኬሽን ጽ/ቤቱ በሚኒስትሮች ምክርቤት ደንብ ቁጥር 158/2001 ሲቋቋም በመንግስትና በሕዝቡ መካከል ቀልጣፋ ውጤታማ የመረጃ ፍሰት እንዲኖር ማስቻል አንዱና ዋና ዓላማው ያደረገ ቢሆንም በተግባር ግን የሰለጠኑና ልምድ ያካበቱ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎችን የአመለካከት ችግር አለባቸው በሚል በማባረርና በማንሳፈፍ ካድሬዎችን በለብለብ ስልጠና ሲመድብ ቆይቷል፡፡ ዘርፉ ልምድና በቂ ስልጠና በሌላቸው ካድሬዎች በመያዙ በመረጃ አሰጣጥ በኩል ያለው ችግር እንዲባባስ ምክንያት ሆኗል፡፡
ጽ/ቤቱ የመደባቸው ካድሬዎች በተለይ በማህበራዊ ድረገጾች አጠቃቀም ደካማ በመሆናቸው ምክንያት ሚኒስትሩ አቶ ሬድዋን በሰበሰቡዋቸው ቁጥር ከፍተኛ ብስጭት የኢህአዴግን አቁዋም እንኩዋን መናገር የማይችሉ በማለት እስከመዝለፍ ደርሰዋል፡፡
የዜና ምንጮቻችን እንደጠቆሙት በአዲስአበባ ቦሌ አካባቢ በሚገኘው ዋሽንግተን ሆቴል ባካሄደው ስልጠና ካድሬዎቹ እንደፌስ ቡክና ቲዎተር ባሉ ማህበራዊ ድረገጾች ላይ እንዴት መጠቀም እንደሚችሉና የመ/ቤታቸውንና የመንግስትን አቋም ከማስረዳት ባለፈም ጸረ መንግስት አቋም ያላቸውን መረጃዎች በማጣጣልና በማስተባበል ረገድ የበኩላቸውን የተከላካይነት ሚና እንዴት እንደሚወጡ በመሰልጠን ላይ ናቸው። በተለይ የማህበራዊ ድረገጾች መንግስትን በሚቃወሙ ሃይሎች ሙሉ በሙሉ ቁጥጥር ስር እንደወደቀ የአቶ ሬድዋን ቢሮ የሚያምን ሲሆን ይህን ለመመከት የሚያስችል ብቃት ያለው የኮምኒኬሽን ባለሙያ ባለመኖሩም ካድሬዎቹ በተደጋጋሚ ወቀሳ ሲሰነዝርባቸው መቆየቱን ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ለዘጋቢያችን ተናግረዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የአንዳንድ የፌዴራል መ/ቤት ተቋማት የህዝብ ግንኙነት ከፍተኛ ካድሬዎች በተለይ በፌስቡክ ፈራተባ እያሉ መረጃዎችን መልቀቅና በሚጻፉ የተለያዩ ጉዳዮች አስተያየት መሰንዘር በመለማመድ ላይ ናቸው፡፡
Thursday, 16 October 2014
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሕዝብ ወገንተኝነቱን የሚያሳይበት ወቅት አሁን ነው!
ዘረኛውና ፋሽስታዊው የህወሓት አገዛዝ የኢትዮጵያን መከላከያ ሠራዊት በዘርና በፓለቲካ ወገንተኝነት በመከፋፈል ሹመቱና ጥቅማ ጥቅሙን ለራሱ ወገን፣ ችግሩንና መከራዉን ግን ለሌላው ኢትዮጵያዊ ያደለ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም መሠረት ሳይማሩና ሳይሰለጥኑ የጄኔራልነት ማዕረጎችን በሙሉ ሰብስበው የወሰዱት የህወሓት አባላት መሆናቸው የአደባባይ ሚስጢር ነው።
በወያኔ መዳፍ ውስጥ እየተሰቃየች ባለችው ኢትዮጵያችን ውስጥ በዘርም ይሁን በፓለቲካ አመለካከት ከህወሓት የተለዩ ኢትዮጵያዊያን ቢማሩም ቢሰለጥኑም ለከፍተኛ አመራርነት እንደማይበቁ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ያየነው ነው። አገዛዙ ቅራኔ ውስጥ በገባባቸው ቦታ ሁሉ እየዘመቱ ሕይወታቸውን እየገበሩ ያሉት ግን በመካከለኛና ዝቅተኛ ማዕረጎች ያሉ ኢትዮጵያዊያን መኮንኖችና ብዙሃኑ የሠራዊቱ አባላት የሆኑ ወታደሮችናቸው። ብዙሃኑ የሠራዊት ክፍል አለቆቹን ከመጠበቅ ባለፈ ድምጹን ከፍ አድርጎ ለመናገር እንኳን የማይፈቀድለት ሎሌ ተደርጓል።
ለኢትዮጵያዊ ወታደር ለህወሓት ሎሌ ከመሆን በላይ የሞት ሞት የለም። ብዙሃኑ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊቱ አባላት በጥቂት የወያኔ ሹማምንት የሚረገጥ መሆኑ የሠራዊቱን አባላት የግል ስብዕና ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የሠራዊቱን ክብር ይነካል። የሠራዊታችን የህወሓት አገልጋይ መሆን የምንወዳት አገራችን ኢትዮጵያን ያዋርዳል። ይህ ዉርደት በዚህ ሁኔታ መቀጠል የለበትም።
ከእንግዲህ ጄኔራሎችና ሌሎችም የበላይ አዛዦች ሁሉ የአንድ አካባቢ ተወላጆች በሆኑበት ሠራዊት ውስጥ ተስማምቶ መኖር መቀጠል እያንዳንዱን የመከላከያ ሠራዊት አባል ሊያሰፍር ይገባል። የህወሓት ጄኔራሎች ጮማ በውስኪ ሲያወራርዱ፤ በህንፃዎች ግንባታ፣ በባንኮች ንግድ፣ በግብርናና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ተሰማርተው ቢዝነሳቸውን ሲያጧጥፉ፣ ምስኪኖቹ የሠራዊቱ አባላት በኦጋዴን፣ በአፋር፣ በኦሮሚያ፣ በጋምቤላ፣ በአማራና በሌሎች የአገሪቱ ግዛቶች እየተወረወሩ ወገኖቻቸውን የሚፈጁበት ሥርዓት ማብቃት አለበት። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ብዙሃኑ አባላት ቤተሰቦቻቸው በችጋር እየተቆሉ የአዛዦቻቸው ሀብት ጠባቂ መሆናቸው ማክተም አለበት።
የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት የጭለማ ዘመን ታሪክ እያበቃ መሆኑን የሚጠቁሙ ምልክቶች እየታዩ ነው። መሣሪያዎቻቸውን እንደያዙ የነፃነት ኃይሎችን የሚቀላቀሉ የሠራዊቱ አባላት ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨረመ መጥቷል። ሠራዊቱ ከሕዝብ ጎን እንደሚቆም ውስጥ ውስጡን የሚላኩ መልዕክቶች እየተበራከቱ መጥተዋል። ይህ አበረታች ዜና ነው፤ ግን በቂ አይደለም። ወያኔን ከውስጥም ከውጭም የምናጣድፍበት ጊዜው አሁን ነው። የነፃነት ኃይሎችን መቀላቀያ ጊዜ አሁን ነው፤ በሠራዊቱ ውስጥም በህቡዕ መደራጃ ጊዜ አሁን ነው። ይህን ጊዜ መጠቀም ብልህነት ነው።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ጥቂት የህወሓት ጥጋበኞች በብዙሃኑ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ላይ የሚያደርሱት በደል ማብቃት አለበት ይላል። ግንቦት 7፡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት በሙስና የደለቡት፣ ትዕቢተኛና ጨካኝ መሪዎቻቸው ፍጹም ኢትዮጵያዊ ባህርይ የሌላቸው ፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች እንደሆኑ በመረዳት በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ክንዱን እንዲያነሳባቸው ጥሪ ያደርጋል። ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ሕዝብም የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አንድ ወጥ እንዳልሆነ እና በመካከለኛና ዝቅተኛ ደረጃ ያሉ መኮንኖችና አብዛኞዎቹ ወታደሮች የሕዝብ ወገን መሆናቸውን እንዲገነዘብ ያሳስባል። “አብረን ነው ዘረኛውና ፋሽስቱን ወያኔን ከኢትዮጵያ ጫንቃ ላይ አውርደን የምንጥለው” ስንል አብዛኛው የመከላከያ ሠራዊታችን ኢትዮጵያዊ ወገናችን እንደሆነ እና በወደፊቷ ኢትዮጵያ ግንባታ ውስጥም ጉልህ ሚና እንዲጫወት የምንፈልግ መሆኑን ግልጽ ማድረግ እንሻለን። የመከላከያ ሠራዊቱም የሕዝብ ወገንተኝነቱ በተግባር እንዲያሳይ ጥሪ እናደርጋለን። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት የሕዝብ አካል ነው፤ የሕዝብ ወገናዊነቱ በተግባር የሚያሳይበት ትክክለኛ ጊዜ ደግሞ አሁን ነው እንላለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!
Sunday, 5 October 2014
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የያዘችውን ፓሊሲ ትመርምር
መስከረም 15 ቀን 2007 ዓም፣ የዩ. ኤስ. አሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦቦማና ባልደረቦቻቸው በአንድ በኩል ኃይለማርያም ደሣለኝና አለቆቹ በሌላ በኩል ሆነው የሁለትዮሽ ስብሰባ ተደርጎ ነበር። በዚህ ስብሰባ ላይ ፕሬዚዳንት ኦባማ ያደረጉት ንግግር የዲፕሎማሲ ጨዋነት ከሚጠይቀው ርቀት በላይ ተጉዘው ሸሪኮቻቸው ባልሠሯቸው ጀብዶች ማሞገሳቸው አሳዝኖናል። ፕሬዚዳንት ኦባማ ከላይ በተጠቀሰው ቀን ያደረጉት ንግግር ላይ በርካታ ስህተቶች፣ ህፀፆችና ግድፈቶች የያዘ ከመሆኑም በላይ አንዳንዱ አስተያየት የኢትዮጵያዊያንን ክብር የሚነካ ሆኖ አግኝተነዋል።
ፕሬዚዳንቱ ንግግራቸውን የጀመሩት “ኢትዮጵያ በዓለም ከሁሉም በላይ በከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ ያለች አገር ነች“ በሚል ዓረፍተ ነገር ነበር። የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ ጽ/ቤት የፈጠራ ቀመሮች በዓለም ባንክ በኩል ዞረው በሚስ ሱዛን ራይስ ተቀነባብረው በባራክ ኦባማ አንደበት መስማት የሚያሳፍር ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ ኦባማ የተናገሩትን ዓረፍተ ነገር ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥና ራድዮ ደጋግሞ ሰምቶ ሰልችቶታል። ኦባማ፣ ይህ የተሰለቸ ዓረፍተ ነገር በእሳቸው አንደበት ሲነገር ስለሚሰጠው ትርጉም ጥቂት ቢያስቡ ኖሮ ለእሳቸውም ለአሜሪካም የተሻለ ነበር ብለን እናምናለን። “በአንድ ወቅት ራሷን መመገብ ያቅታት የነበረችው አገር ዛሬ ከፍተኛ እድገት የሚታይባት ሆናለች፤ አሁን የግብርና ብቻ ሳይሆን [የኤሌክትሪክ] ኃይልንም በመሸጥ በቀጠናው ቀዳሚነት ይዛለች” ሲሉ ያሞካሿት ኢትዮጵያን ኢትዮጵያዊያን የማያውቋት መሆኑን፤ እሳቸው የሚያወድሷት ኢትዮጵያ በህወሓት ፕሮፖጋንዳ እንጂ በመሬት ላይ የሌለች መሆኑን ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ማወቅ ነበረባቸው። በአንፃሩ የእውነተኛዋ ኢትዮጵያ 70% ሕዝብ በድህነት ወለል በታች በሆነ ኑሮ ሕይወቱን እየገፋ እንደሆነ፤ የሚሊዮኖች ኢትዮጵያዊያን የእለት ጉርስ ምንጭ የአሜሪካና የአውሮፓ አገሮች እርዳታ መሆኑን ፕሬዚዳንት ኦባማ አያውቁም ማለት ይከብዳል። ፕሬዚዳንት ኦባማ የተናገሩለት የመብራት ኃይልም ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተስፋ ተረት መሆኑን፤ ዛሬም የኢትዮጵያዊው የምሽት ኑሮ የሚገፋው በባትሪ፣ በሻማና በኩራዝ መሆኑን ፕሬዚዳንት ኦባማ አያውቁም ማለት ያስቸግራል።
ፕሬዚዳንት ኦባማ ከተናገሩት ውስጥ ትርጉም የሚሰጥ ነገር ቢኖር ስለ “ሰላም ማስከበር” የተናገሩት ነው። የህወሓት አገዛዝ፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትን ገንዘብ ባለበት እና አሜሪካ ወደ ፈለገችው ቦታ ሁሉ የሚልክ መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም የጦሩ የሰላም ማስከበር ሥራ ማሞካሸታቸው የሚጠበቅ ነው። እንዲያውም የፕሬዚዳንቱ ሙሉ ንግግር የተቃኘው ከዚህ አቅጣጫ ይመስላል። እንደዚያ ባይሆን ኖሮ የራሳቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያወጣውን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሪፖርትን ውድቅ የሚያደርግ ነገር ባልተናገሩም ነበር። አንዳችም ነፃ ተቋማት በሌሉበት አገር ውስጥ ፍትሃዊ ምርጫ የሚባል ነገር ሊኖር እንደማይችል አውቀው ቀዳሚው ጥያቄዓቸው የሰብዓዊ መብቶች መከበር እና የነፃ ተቋማት ግንባታ ጉዳይ ባደረጉት ነበር። ፕሬዚዳንት ኦባማ ስለኢትዮጵያ ተጨንቀው ቢሆን ኖሮ የራሳቸው ስቴት ዲፓርትመን የዘንድሮውን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሪፓርት ያስታውሱ ነበር። ሪፓርቱን በማስታወሳቸው ብቻ በግፍ እየታሰሩ ስላሉት ዜጎች፣ በኦጋዴን፣ በኦሮሚያ፣ በጋምቤላ፣ በአፋር እና በአማራ እየተጨፈጨፉ ስላሉ ዜጎች፣ ስለ መሬትና የሀብት ዘረፋ፣ ስለፍትህ እጦት፣ ስለ ተቋማዊ ዘረኝነት እና ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች እንዳነሱ ይቆጠር ነበር፤ ምክንያቱም ያ ሪፓርት የያዘው ይህንን ሁሉ ነው። ፕሬዚዳንት ኦባማ ግን የንግግራቸው ግብ ዘማች ወታደር ማግኘት በመሆኑ የራሳቸውን የስቴት ዲፓርትመንት ሪፓርት ትተው የወያኔን ሪፓርት ይዘው የቀረቡ አስመስሎባቸዋል። ይህ አካሄድ አሜሪካ ወደማትፈልገው የጦር አረንቋ የሚላኩ የሠራዊት አባላት ሊያስገኝ ቢችልም የሚያስከትላቸው ጉዳቶችም መታየት ነበረባቸው። የንግግራቸው ፈጣን አሉታዊ ውጤት ለማየት ቀናትም አልፈጀም፤ እነሆ በኦባማ አይዞህ ባይነት የተነቃቁት የህወሓት ገዳዮች ከኢትዮጵያ አልፈው በአሜሪካ ምድርም በኢትዮጵያዊያን ላይ መተኮስ ጀምረዋል።
የኦባማ ንግግር ትኩረት የፀጥታ ጉዳዮች ሆኖ ኢኮኖሚ የግኑኝነት ማሳለጫ ሆኖ ቀርቧል፤ የሰብዓዊ መብት አጠባበቅና የዲሞክራሲ ጉዳዮች ደግሞ ፈጽመው ተገፍተው ወጥተዋል። ይህ ንግግር አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የምትከተለውን ፓሊሲ አመላካች ነው።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በፀጥታ ጉዳይም ቢሆን አሜሪካ የያዘችው አቋም በረዥም ጊዜ የኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን የአሜሪካን ጥቅም የሚጎዳ ነው ብሎ ያምናል። ኢትዮጵያ ለአሜሪካ ከወታደር ምንጭነት በላይ የምታገለግል አገር ናት። ኢትዮጵያ ውስጥ ከራሱ ሕዝብ ጋር የታረቀ መንግሥት መኖር ለቀጠናው ሰላም እና ብልጽግና ወሳኝ ከመሆኑም በላይ የቀጠናው ሰላምና ብልጽግና የአሜሪካም ስትራቴጂያዊ ጥቅም ነው ብለን እናምናለን። የአጫጭር ጊዜ ጊዜዓዊ ጥቅሞችን ብቻ በመመልከት አምባገነኖችን መደገፍ አሜሪካን ምን ያህል ውድ ዋጋ እያስከፈላት እንደሆነ በዓይኖቻችን እያየነው ያለ ሀቅ ነው። አሜሪካ አምባገነኖችን መደገፏን ከቀጠለች ፈጥኖም ይሁን ዘግይቶ የምታገኘው እስካሁን ስታገኝ የነበረውን ውግዘትና የጽንፈኞች መጠናከር ነው። አሜሪካ የተሳሳተ ፓሊሲ በያዘችባቸው አገሮች ሁሉ ግንባር ቀደም ተጎጂዎች ለዘብተኞችና ዲሞክራቶች ሲሆኑ እየተጠናከሩ የሚመጡት ደግሞ ጽንፈኖች ናቸው። አሁንም አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የያዘችውን ፓሊሲ የአገሪቱን የዲሞክራሲ ኃይሎችን የሚያዳክም እና ጽንፈኛ ኃይሎችን የሚያበረታታ እንደሆነ ከወዲሁ ሊጠን ይገባዋል።
ዩ. ኤስ አሜሪካ የምትመራባቸው የነፃነት፣ የእኩልነትና የፍትህ እሴቶች የግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እሴቶችም ናቸው። ኢትዮጵያዊያን እንደ አሜሪካ ዜጎች ሁሉ ፍትህን፣ ነፃነትን፣ እኩልነትንና ዲሞክራሲን ይሻሉ፤ እነዚህ መሻት ደግሞ መብታቸው ነው ብሎ ግንቦት 7 ያምናል፤ ለዚህም ይታገላል። አሜሪካ ይህን ትግል ማገዝ ይገባታል። በተግባር የምናየው ግን የዚህ ተቃራኒ ነው። አሜሪካ ለአጫጭር ጊዜ ጥቅም ስትል ከአምባገነን ኃይሎች ጋር ማበሯ የዓላማ ተጋሪዎቿን እያዳከመ መሆኑ የወቅቱ የዓለም ሁኔታ የሚመሰክረው ሀቅ ነው። በኢትዮጵያ ላይ እየተከተለችው ያለው ፓሊሲው ተመሳሳይ የረዥም ጊዜ መዘዝ እንዳያመጣ ያሰጋል። ይህ እንዳይሆን እርምት የሚገባው አሁን ነው።
ስለሆነም፣ ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ዩ. ኤስ. አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የያዘችውን ፓሊስ እንደገና እንድትመረምር እና ዘረኛና አምባገነኑን የህወሓት አገዛዝን መርዳት እንድታቆም አበክሮ ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
Saturday, 4 October 2014
ደቡብ ሱዳን የኢትዮጲያን ተቃዋሚዎች ልትረዳ ነው
Oct 3, 2014(Nyamilepedia) — An insider, from within the inner circle of South Sudan security organ, alleged that he, in a team supervised by Akol Koor, the Director of Internal Security Bureau, met Gen. Thokwaath Pal, the leader of the rebel Ethiopian Unity Patriotic Front (EUPF) in mid September 2014.
The insider alleged that the main objectives of the meeting was to seal a new deal that would strengthen the Ethiopian rebels groups to destabilize the SPLA rebels’ main military training centers in Maiwut and Pagak at the eastern corridor of South Sudan – Ethiopia border.
According to the insider, Gen.Thokwaath has been tasked to establish links with other rebel groups within Ethiopia to form a coalition that will fight for a regime change and destabilize South Sudan Peace Process in Bahir Dar.
According to the insider, director Akol Koor has issued One Million ($1,000,000) US Dollar to Ethiopia Rebel groups to equip and set up their operation centers at South Sudan-Ethiopian border.
The intelligence alleged that Juba has promised Gen. Thokwaath a sufficient financial and military supports. He said that military garrisons will be set up at the border to detach any military support from Ethiopian government to South Sudan rebels.
Gen. Thokwaath is also expected to cut any supply routs and recruitments from Gambela Refugees camps in Ethiopia to South Sudan. This would allegedly benefits the regime as it expected to lure the Eastern Jikany to support South Sudan government.
South Sudan government delegation, according to Michael Makuei Lueth’s interview on BBC focus on Africa, has lost truth in TROIKA, Ethiopia and the Ethiopian Ambassador, Seyoum Mesfin, who leads South Sudan Peace Talks. Hon Makuei recently calls on IGAD to relocate the peace process to Kenya and change the chief mediator.
According to Michael Makuei Lueth, Ethiopia and TROIKA partners support regime change in South Sudan. Mr. Lueth fears that unless the mediation is relocated to Kenya and led by the Kenyan Envoy, General Lazarus Sumbeiyo, the peace process may never yield an agreement.
Salva Kiir government allied with Ugandan and Sudanese rebels against the insurgents in Greater Upper Nile. Four rebels’ factions that are fighting for regime change in Sudan joined South Sudan civil war in December 2013.
The Government of South Sudan signed military cooperation with Egypt amid allegations that Ethiopia support SPLA rebels, under the former vice president, Dr. Riek Machar Teny. The agreement has allegedly given Egypt a green light to set up a military base in South Sudan, a move that is expected to throw off Ethiopia’s mega project, the Grand Ethiopian Renaissance Dam.
Monday, 29 September 2014
የታጋይ አንደርጋቸው ጽጌ ጉዳይ በአውሮፓ ህብረት ምክርቤት ኮሚሽን ውይይት ተደረገበት፤ በአስቸኮይ እንዲፈታም ጠይቀዋል።
ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ በአምባገነኑ ወያኔ እጅ ወድቆ መሰቃየት ከጀመረ 3 ወራት አልፈዋል። ባለፉት ቀናት የአውሮፓ ህብረት የሰበአዊ መብት ም/ቤት በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ውይይት አደርገዋል ። አንዳርጋቸው የፖለቲካ እስረኛ እና ለዲሞክራሲ፣ ለነጻነት፣ ለመልካም አስተዳደር እና ሰበአዊ መብት መከበር የሚታገል የግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር ሲሆን ባስቸኮይ ተለቆ ወደ እንግሊዝ እንዲመለስ ኮሚሸነር ተናግረዋል፡፡የተከበሩ አና ጎሜዝ አንዳርጋቸው ብቻ አይደለም በርካታ ኢትዮጵያኖች ታስረዋል ብሎግ ዘጠኝ፣ ጋዜጠኞች፤ ፖለቲከኞች ሁሉም ካለ ምንም ምክንያት መፈታት አለባቸው። የኢትዮጵያን ፓርላማ ባለፈው ሂጄ አይቸዋለሁ በጣም የሚገርም ነው የፖለቲካ እስረኛ ሳይሆን ሽብርተኞች ናቸው ያሉን ሲሉ ከአንድ መንግስት የማይጠበቅ ነው። እስክንድር ነጋ ሽብርተኛ ሳይሆን አለም አቀፍ የብእር ተሸላሚ ነው። ብሎግ 9 ጸሃፊያን፣ ጦማሪያን ናቸው። አንዳርጋቸው ጽጌ የፍትህ ታጋይ ነው። ታዲያ እንዴት ነው የኢትዮጵያ መንግስት ህግን የሚተረጉመው ሲሉ ተናግረዋል።
ኮሚሽኑ በሁለት ወር ውስጥ ይህን ጉዳይና የኢትዮጵያን ሰበአዊ መብት በተመለከተ እና የአንዳርጋቸው ጽጌን ጉዳይ የሚመለከት ኮሚቴ እንዲሰየም እና እንደገና እንደሚወያዩበት የወሰኑ ሲሆን የአቶ አንዳርጋቸውን በተመለከተ አሳሳቢ በመሆኑ ከእንግሊዝ መንግስት ጋር በመሆኑ ለብቻ በሚቀጥሉት እናየዋለን ሲሉ ዘግተዋል።
በዚሁ ስብሰባ የኢትዮጵያ መንግስት ተወካይ ቀርበው አሁንም የተለመደ ማስተባበያ ሰጥተዋል። እኛ ምንም አይነት ህግ አልጣስንም ብለዋል።
Friday, 19 September 2014
በህወሓት አገዛዝ በኦጋዴን ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን የጅምላ ግድያ በጽኑ እናወግዛለን!!!
የአገራችን የኢትዮጵያን በትረ ሥልጣን በጠመንጃ ኃይል የተቆጣጠረው ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ የሥልጣን እድሜውን ለማራዘም በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየወሰደ ያለውን እሥራትና ግድያ አጠናክሮ መቀጠሉን የሚያጋልጡ ማስረጃዎች በየጊዜው ከራሱ ከአገዛዙ እየሾለኩ በመውጣት ላይ ናቸው።
መስከረም 5 ቀን 2007 ዓም በኢትዮጵያ ሳተላይት ቴለቪዥን በምስል ተደግፎ የቀረበው በኦጋዴን ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው ጭፍጨፋ ከነዚህ ማስረጃዎች አንዱ ነው ።
የወያኔን አገዛዝ ይቃወማሉ የተባሉና በኦጋዴን ክልል ከሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚዎች ጋር ንኪኪ አላቸው የተባሉ እነዚያ የጅምላ ጭፍጨፋ ሰለባ የሆኑ ምስኪን ዜጎች አስከሬን መሬት ለመሬት እየተጎተተ አንድ ቦታ እንዲከማች ሲደረግ፤ አስከሬኑን ለመሰብሰብ ከታዘዙት የአካባቢው ነዋሪዎች አንዱ የገዛ ወንድሙ አስከሬን ከሚጎተተው መሃል እንደነበረ መስማት ህሊናን የሚሰቀጥጥና የወያኔ የጭካኔ እርምጃ አቻ የሌለው ደረጃ ላይ መድረሱን የሚያመላክት ነው።
በደርግ ዘመን ቤተሰብ የተገደለበትን ሰው አስከሬን ለማግኘት የጥይት ዋጋ ለመክፈል ይገደድ ነበር በማለት ሥርዓቱን በነጋ በጠባ የሚወነጅል አገዛዝ ከሚወነጅላቸው ሥርዓት በባሰ በኦጋዴን የገደለውን ንጹህ ዜጋ አስከሬን የገዛ ወንድሙ መሬት ለመሬት እንዲጎትተው አድርጓል። በዚህም ህወሓት በሰብዓዊነት ላይ ከቀደምቶቹ ሁሉ የከፋ የሚሰቀጥጥ ወንጀል ፈጽሟል። ቀደም ሲል በበደኖ፤ በአርሲ፤ በአርባ ጉጉ፤ በሃዋሳ ፤ በጋምቤላ እና ድህረ ምርጫ 97 በአዲስ አበባና ሌሎች የአገሪቱ ከተሞች ነዋሪዎች ላይ በወያኔ ልዩ ትዕዛዝ ተመሳሳይ የጅምላ ጭፍጨፋዎች ተካሂደዋል። ይህ ሁሉ ወንጀል እየተፈጸመብን አስከዛሬ ወያኔን በጫንቃችን ተሸክመን ለመኖር የተገደድነው እነዚሁ ጥቂት ዘረኞች ሕዝባችንን በዘር፤ በቋንቋና በሃይማኖት በመከፋፈላቸው አንዱ የኅብረተሰብ ክፍል ሲጠቃ ሌላው በዝምታ የሚመለከትበት ሁኔታ በመፈጠሩ ነው።
ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ወያኔ በኦጋዴን ሕዝብ ላይ የፈጸመውን ይህንን አረመኔያዊ እርምጃ አጥብቆ ያወግዛል። ጊዜው ሲደርስ የዚህ ወንጀል ፈፃሚዎች ለፍርድ መቅረብ አለባቸው ብሎ ያምናል። ስለሆነም ወያኔ ሕዝባችንን አቅም ለማሳጣት ላለፉት 23 አመታት በኅብረተሰባችን መካከል የገነባውን የጥርጣሬና የጥላቻ ግንብ በመናድ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በኦጋዴንና በሌሎች የአገራችን ክፍሎች ወገኖቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ሰቆቃና እልቂት ለማስቆም እንዲችሉ የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል።
ኦጋዴን ውስጥ ለፈሰሰው የንጽሃን ደምና በሰብዓዊነት ላይ እየተፈጸመ ላለው ወንጀል ተጠያቂው ሥልጣንን በኃይል የሙጥኝ በማለት በአገርና በሕዝብ ሃብት ዘረፋ ላይ የተሰማራው ጥቂት የህወሃት አመራር መሆኑ አያጠያይቅም። ይህንን ወንጀለኛ ቡድን ለፍርድ ለማቅረብ ንቅናቄዓችን ግንቦት 7 የሚያደርገውን ሁለገብ ትግል ለፍትህ ለነጻነትና ለዲሞክራሲ የቆመ ኢትዮጵያዊ ሁሉ እንዲቀላቀል በዚህ አጋጣሚ ጥሪ ቀርቦለታል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
Sunday, 7 September 2014
የኢህአዴግ አባላት በድርጅታቸው ላይ ጥያቄዎችን ማንሳት ቀጥለዋል
በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለከተሞች በመካሄድ ላይ ባለው የኢህአዴግ አባላት ስብሰባ ፣ አባላቱ ዛሬም በርካታ ጥያቄዎችን ሲጠይቁ መዋላቸውን ከውስጥ ምንጮች የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ዛሬ ከሰዓት በኋላ በአባላቱ ከተነሱት ጥያቄዎች መካከል፡- ” የኢትዮጵና የኤርትራ ህዝቦች የማይነጣጠሉ የአንድ ሃገር ዜጎች ሆነው ሳለ በመሪዎች አለመግባባትና ሽኩቻ በመለያየታቸው እስከዛሬ ድረስ እየተላቀሱ ይገኛሉ፤ ይህም የሆነው በኢህአዴግም አስተዋፆ ጭምር ነው፤ አሁንም ቢሆን ከኛ ጋር መስማማት ከፈለጉ በራችን ክፍት ነው የምትሉት ከልባችሁ ነወይ?” የሚለው ጥያቄ ሰፊ ሰአት ወስዶ ማከራከሩ ታውቋል።
በሃይማት አክራሪነት ጉዳይ ለተነሱት ጥያቄዎች ደግሞ ” ሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ ሰልፍ በጠራበት ጊዜ ሰልፈኛው መስኪድ አካባቢ ሲደርስ ሙሉ ለሙሉ ለጸሎት ወደ መስኪድ እንደገባ አረጋግጠናል፤ ስለሆነም
” መንግስት ሁሉንም ሚዲያዎች እንደጥፋተኛ ቆጥሮ ጋዜጦችና መጽሔቶችን እንዳለ ከገበያ ማስወጣቱ እኛ አባሎቹ የኢህአዴግን ክፍተት የምናውቅበት መንገድ ተዘግቷል፤ ኢህአዴግ ለስራ አጥ ዜጎች የስራ ዕድል እፈጥራለሁ እያለ በአንፃሩ ግን የስራ ዕድል የሚፈጠርላቸው ዜጎች በአባልነት ላይ የተመረኮዘ ለምን ይሆናል? በታችኛው ህብረተሰብ አካባቢ በብልሹ አሰራር ውስጥ ገብተው ከፍተኛ ሙስና የሰሩና በህዝቡ የተገለሉ ሰዎች ተሸፍነው ወደ ላይ ሲወጡ ሹመት ይደረብላቸዋል ይህ ተገቢ ነወይ?” የሚሉ ጥያቄዎችም ተነስተዋል።
የአዲስ አበባ የመሬት ወረራ ጉዳይም ሰፊ አጀንዳ የነበረ ሲሆን፣ ኢህአዴግ በሰላማዊና ጠንካራ ተቃዋሚዎች ላይ የያዘው አቋምም ትችት አዘል ጥያቄ አስነስቶበታል።
የዛሬውን የፕላዝማ ውይይት የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታው መርተውታል።
ትናንት ከሰአት በሁዋላ በነበረው የውይይት ጊዜ ደግሞ ” ኢህአዴግ ለሃገሪቱ ስጋት ብሎ ከለያቸው የፖለቲካ ጉዳዮች ውስጥ ዋነኛ ያላቸው የሃይማኖት አክራሪነት ወይም ጽንፈኝነት እና የመልካም አስተዳደር እጦት ቢሆኑም፣ የ ኑሮ ውድነቱ በስጋትነት ሊካተት ይገባል” የሚል አስተያየት ቀርቧል።
የደመወዝ ጭማሪው አርኪ አለመሆኑና እንዳውም የበለጠ ህዝቡንና የመንግስት ሰራተኛውን ለችግር መዳረጉም በአባላቱ ተነስቷል።
ሰልጣኞቹን በሚሰለጥኑበት ቦታ ጥያቄዎች ሲነሱ እዚያው በህዋሳቸው በሰልጣኞቹ እንዲመለስ በማሰብ በህዋስ ማደራጀት መጀመሩን፣ ሰልጣኞቹ የመድረኩን የፕሮፓጋንዳ ገለፃ ብዙ ትኩረት ሳይሰጡ የጥያቄና መልስ ክፍለ ጊዜ ሲደርስ ግን በንቃት ጥያቄ የሚያነሱ ሲሆን፣ አንዳንዳ ጥያቄዎችን ከውይይሩ ጋር ግንኙነት የላቸውም ወይም ጥያቄውን ወደ ኋላ ላይ ማንሳት ትችላላችሁ በሚል እንደሚታለፉ የውስጥ ምንጮች ገልጸዋል።
ዘግይቶ በደረሰን ዜና ደግሞ የግንቦት 7 ድርጅት አጀንዳ የነበረ ሲሆን በአንዳንድ አባላት ዘንድ ግንቦት 7 ከውጭ መንግስታት ጋር በማበር በሀገር አብዮት እንዲነሳ እየሰራ ነው ሲሉ ሌሎች አባላት ደግሞ ግንቦት 7 አሸባሪ ከተባለ ለምን የአሜሪካ መንግስት አሳልፎ አይሰጥም? እናንተ እንደምትሉት አሸባሪ ቢሆን ኖሮ ያስሩዋቸው ነበር ብለው ተከራክረዋል፡፡ አወያዮቹም ከአሸባሪዎች ጋር መገናኘት የለባችሁም፣በሀገር የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚዎች አብረው እየሰሩ እንደሆነ ለአባላቱ የገለጹ ሲሆን ንክኪ እንዳይኖራችሁ ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡
በኢህአዴግ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የታየው ግምገማ መነሻ፣ በቅርቡ ኢህአዴግ መዳከሙን የተመለከተ ግምገማ ከተደረሰ በሁዋላ ነው። ይህን ተከትሎ ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ ፖሊሶች፣ የህግ ባለሙያዎች በመንግስት ፖሊሲ ዙሪያ ስልጠና ሲሰጥ ቆይቷል። በስልጠናው ላይ የተነሱትን ጥያቄዎች የኢህአዴግ አባላት እንዲመክቷቸው በሚል እየተሰጠ ያለው ስልጠና ያልተጠበቁ ጥያቄዎችን ማስነሳቱ፣ ከፍተኛ አመራሮችን ሳይቀር በእጅጉ ማስገረሙን ምንጮች አክለው ገልጸዋል።
“እዚህ የምናደርገው ስብሰባ በኢሳት ይዘገባል ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ ? ” በሚል አመራሩ እየተነጋገረበት መሆኑንም ታውቋል።
ብአዴንም መረጃዎች እየወጡ ተቸግረናል በሚል ትናንት በጀመረው ግምገማ ማንም ሰው ሞባይል ስልኮችን ይዞ እንዳይገባ ከልክሏል።
Subscribe to:
Posts (Atom)





