Friday, 30 January 2015

US urges Ethiopia to ensure fair trial to bloggers and journalists

January 30, 2015 (U.S. Department of State) The United States is concerned by the Ethiopian Federal High Court’s January 28, 2015, decision to proceed with the trial of six bloggers and three independent journalists on charges under the Anti-Terrorism Proclamation. The decision undermines a free and open media environment—critical elements for credible and democratic elections, which Ethiopia will hold in May 2015.US on Ethiopian bloggers We urge the Ethiopian government to ensure that the trial is fair, transparent, and in compliance with Ethiopia’s constitutional guarantees and international human rights obligations. We also urge the Ethiopian government to ensure that the trial is free of political influence and continues to be open to public observation. The use of the Anti-Terrorism Proclamation in previous cases against journalists, activists, and opposition political figures raises serious questions about the implementation of the law and about the sanctity of Ethiopians’ constitutionally guaranteed rights to freedom of the press and freedom of expression. Freedom of expression and freedom of the press are fundamental elements of a democratic society. We call on the government of Ethiopia to support freedom of expression and freedom of the press to demonstrate its commitment to democracy as it approaches its May 2015 national elections.

Tuesday, 20 January 2015

ወያኔ የሚመለመል ወታደር አጣ

ወያኔን የሚከዱ ወታደሮች በየቦታው እየተሰማ ባለበት ባሁኑ ሰዓት የሚመለመል ወታደር መጥፍቱ ምናልባትም ወያኔዎቹ ከፍተኛ የራስ ምታት ሳይሆንባቸው አይቀርም፡፡ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል በተደጋጋሚ የአዲስ ቅጥረኛ ወታደር ማስታወቂያ ቢያወጡም፣ አይደለም የሚመለመል ወታደር ቀርቶ የሚመዘገብ ጠፋ፡፡ እናም ይህንን ችግር ለመፍታት ወያኔ አዲስ ዘዴ ቀየሰ፡፡ ከከተማ እስከ ገጠር ቀበሌ፣ በብረታብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ስም አማላይ ማስታወቂያዎችን አስለጠፈ፡፡ ይህ በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የወጣው ማስታወቂያ የሚመለምለው በሚከተሉት የሙያ ዘርፎች እንደሆነ ይዘረዝራል፡፡ ጄኔራል መካኒክ ኤሌክትሪክሲቲ/ ኢንዱስትሪያል ኤሌክትሪክ ሲቲ/ ኤሌክትሮኒክ /ማካትሮኒክ/ ማሽን ቴክኖሎኪ አውቶ መካኒክ አውቶ ኤሌክትሪክ *የምልመላ መስፈርቱ ‹‹በመከላከያ ሚኒስቴር ለአዲስ ምልመላ ወታደሮች ያስቀመጣቸው የቅበላ መስፈርቶች እንደተጠበቁ ናቸው›› ይላል፡፡ ይህን የማታለያ ዘዴ (አታሎ ወታደር የማድረግ) ወያኔ ብዙ ጊዜ ተጠቅሞበታል፡፡ በኢትዮ – ኤርትራ ጦርነት ጊዜ አስራ ሁለተኛ ክፍል የጨረሱ ተማሪዎችን ‹‹ኑ እናስተምራችሁና ስራ እናስቀጥራችሁ›› ብለው አታለው ከወሰዷቸው በኋላ ጦርነት ውስጥ ማገዷቸው፡፡ ብዙ እናቶችም የደም እንባ አነቡ፡፡ ዘንድሮ ግን ይህ የማታለያ ዘዴ ፈጽሞ ሊሰራላቸው አልቻለም፡፡ ምክንያቱም ይህችን የወያኔ ጨዋታ ህዝቡ በልቷታል፡፡ በገጠር ቀበሌዎች ማስታወቂያውን የለጠፉት አብዛኛውን ፖሊሶች ናቸው፡፡ በስተ-እግር መንገዳቸውም እለቱ እሁድ ስለነበር፣ የተሰበሰቡትን ገበሬዎች ልጆቻቸውን እንዲሰዱ እና ይህ እድልም እንዳያልፋቸው ሰበካ አድርገው ነበር፡፡ ከሰባኪያን ፖሊሶች አንዱ ያለው ግን በጣም ያስቃል፡፡ እንዲህ ነበር ያለው ‹‹እኔ ይህን እድል ባገኜው ኖሮ፣ ዳግም የተፈጠርሁ ያህል እቆጥረው ነበር›› ነበር ያለው፡፡ ያኔ ሁሉም ገበሬዎች ሳቁልሃ! አንዳንዶቹም ‹‹ታዲያ ለምን አትሄድም?›› ሲሉ አሾፉበት፡፡ ጋሽ ፖሊሱ በመጣበት መንገድ አፍሮ ተመለሰ፡፡ በከተማ ማስታወቂያውን ካድሬዎች ሲለጥፉ የከተማው ወጣቶች ከበው ያዩዋቸው ነበር፡፡ አብዛኛዎቹ ስራ አጥ ስለሆኑ የስራ ማስታወቂያ መስሏቸው ነበር ሰፍ ብለው ለጣፊውን ካድሬ ክብብ ያደረጉት፡፡ ማስታወቂያውን አንብበው እንኳ ሳይጨርሱ ‹‹አንተ ለምን አትሄድም›› ሲሉ አምባረቁበት፡፡ እኒህ ወጣቶችና ማስታወቂያውን የለጠፈው ካድሬ ማታ ካራንቡላ ቤት ተገናኙ፡፡ ስለ ማስታወቂው ወሬ ተጀመረ፡፡ እናም ካድሬው ማንንም ሳይፈሩ ‹‹እብድ ይሂድ እንጂ ማንም እንዲሄድ አልመክርም›› ብለውት እርፍ አሉ፡፡ በነገራችን በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ከወጣት እስከ ሽማግሌ ከመንግስት ሰራተኛ እስከ ገበሬዎች የወያኔን የጦር ካምፕ ሳይሆን የአማጺያንን ካምፕ እየተቀላቀሉ ነው፡፡ - See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/3825#sthash.w0PHu4Pi.dpuf

Saturday, 10 January 2015

ሰው በላውን ወያኔን እናጠፋዋለን!!! -ከ-አዲስ ብርሃኑ

ከ-አዲስ ብርሃኑ andargacew Tsigeአንዳርጋቸውን ሳስበው ውስጤ ያለው የኢትዮጵያዊነት ወኔ ይቀጣጠልብኛል። ብርሃን ካለ ጨለማ የለም ብርሃን ከሌለ ግን ጨለማ አለ። አንዳርጋቸው ማለት ለኢትዮጵያዊያን በሙሉ ብርሃን ማለት ነው። የለኮሰው ብርሃን በኢትዮጵያ በሙሉ የሚበራ ብርሃን ነው። አንድአርጋቸው በኢትዮጵያ የለኮሰው ብርሃን የሰላም ብርሃን ነው፣ የፍቅር ብርሃን ነው፣ የቆራጥነት ብርሃን ነው፣ የጀግንነት ብርሃን ነው፣ የአንድነት ብርሃን ነው፣ የትግል ብርሃን ነው። በዚህ ብርሃን ውስጥ የማይጓዝ ማንም ኢትዮጵያዊ የለም። አንድአርጋቸው የኢትዮጵያ ብርሃን!!!የእውነት ብርሃን ጥቅም ያለወጠህ ብርሃን የለኮስከው የነጻነት የትግል ሻማ አንተ ሻማ ሆነህ እየቀለጥክ ብርሃንነትን የለበስክ የኢትዮጵያ ብርሃናዊ ጀግና አንተ ነህ። ወያኔ የፈራው ስራህን ብቻ ሳይሆን ስምህንም ጭምር ነው። አንድነት ለወያኔ አይመቸውም አንድነትን ይፈራል ህብረትን ይጠላል ለያይቶ እና ከፋፍሎ መግዛትን ነው የሚፈልገው። ስለዚህ አንድአርጋቸው ሲባል ያባንነዋል።ወያኔ ለዘረፋው አንድነት አይመቸውም ለተንኮል ስራው አይመቸውም ስለዚህ እንኳን ስራህን ስምህንም አይወዱትም። በኢትዮጵያዊያን ግን ስምህም ተግባርህም ይወደዳል። እዚህ ጋር ነው ቁም ነገሩ በህዝብ መወደድ እና መከበር። የኢትዮጵያ ህዝብ የሰላም ብርሃን የለኮሱትን እና ወደ ብርሃን የሚወስዱትን ብርቅዬ ታጋይ በማይጠፋው በኢትዮጵያዊ መዝገብ ውስጥ ጽፈው ያስቀምጧቸዋል ። ወያኔ እና ከነግብርአበሮቹ ግን ከነስራቸው ይጠፋሉ። ስለ አንዳርጋቸው ጽጌ የተለቀቀውን ቪዲዮ አይቼ በጣም ነውያፈርኩት በቪዲዮ መግቢያው ላይ ምዕራባዊያን የእስር አያያዝ ላይ ትችት ሲያቀርቡ ኢትዮጵያ ውስጥ ግን የእስረኛ አያያዝ በሰላም እንደሆነ እጅ እጅ ያለውን ወሬአቸውን በተለመደ የውሸት ቋንቋቸው ዛሬም ሲደግሙት አይናቸውን በጨው አጥበው በመቅረብ አንዳርጋቸው የሚናገረው ንግግር እራሱ ፈልጎ እንደሆነ አድርጋችሁ አቀረባችሁ። ቪዲዮው ስንመለከት ግን 14 ደቂቃ ባልሞላች ንግግር ውስጥ የአንድአርጋቸው የለበሰው ልብስ በየደቂቃው የቀያየራል ቪዲዮው በየደቂቃው ይቆራረጣል ይበጣጠሳል በዛ ላይ የተላለፈው መልእክት ምን እንደሆነ የማይገባ። ይህንን ቪዲዮ እንደ ኢትዮጵያዊ ሆኜ ሳስበው በጣም አሳፋሪ ነው እንደ ወያኔ አውሬነት ሳየው ደግሞ የምጠብቀው ስለሆነ አይደንቅም የሚገርመው የካድሬዎች ጫጫታ ነው ተንጫጩ እኮ ወይ መንጫጫት በዚህ ዘምን የሚታለል ወይም የወያኔን ስራ የማያውቅ ማንም ኢትዮጵያዊ የለም ኢትዮጵያ ውስጥ የመንግስት አቸባሪ ነው ያስቸገረው። አንዳርጋቸው የለኮሰው የትግል ብርሃን ወያኔን ጥሎ ካልሆነ በስተቀር መቆሚያ የለውም። ወያኔ የአንድአርጋቸውን ጽጌ ቪዲዮ የለቀቀው ግራ ገብቶት ነው ወያኔ ሲጨንቀው ሲጨንቀው ማስተንፈሻ ይፈልጋል ሰሞኑን 3ት የአየር ሃይል አብራሪዎች ከነ ሄልኮፕተር ወደ ኤርትራ መግባታቸው ወያኔን መካዳቸው ያስደነገጠው በተጨማሪም 4ት የአየር ሃይል የተዋጊ አብራሪዎች ወደ ኬኒያ መግባታቸው እና የመከላከያ ሰራዊት ከነ ትጥቁ እየከዳቸው ስለሆነ የመውደቂያው ዋዜማ ላይ መሆኑን ስላወቀው ስለደነገጠ ማስተንፈሻ ስለፈለገ የህዝቡን ሃሳብ ለመበተን በጣም አሳፋሪ እና የተቆራረጠ በዛ ላይ ሃሳቡ ግልጽ ያልሆነ ቪዲዮ ለመልቀቅ ተገደዋል። አሁን ወያኔ በሚደሰኩረው ዲስኩር ዲስኩር ተታሎ ግዜ ሰጥቶ የሚያወራ ቢኖር ወያኔ እና ካድሬዎች ብቻ ናቸው። እኛ ግን አንዳርጋቸው በለኮሰው የብርሃን የትግል ጉዞ ተጉዘን ወያኔን ለመደምሰስ ቆርጠን ተነስተናል። ወያኔ ሆይ አሁን የዘራኽውን ማጨጃህ ሰዓት ላይ ነህ። የኢትዮጵያ ህዝብ የተገደለበት የቆሰለበት የተደበደበበት የተሰደደበት የተረገጠበት የተናቀበት ግዜ አብቅቶ ኢትዮጵያዊው ቁጭቱን ለከፍል ቆርጦ ተነስቷል። ህዝብ ያቸንፋል ወያኔ እና ካድሬዎች ለአንደ እና ለመጨረሻ ግዜ ይጠፋሉ። ድል ለኢትዮጵያዊያን!!!