Saturday, 19 July 2014
U.S. State Department deeply concerned about charges on Zone 9 Bloggers
Africa: Zone 9 Bloggers Charged by Ethiopian Court for Terrorism
07/18/2014 06:08 PM EDT
Zone 9 Bloggers Charged by Ethiopian Court for Terrorism
Press Statement
Jen Psaki
Department Spokesperson
Washington, DC
July 18, 2014
The United States is deeply concerned by the Ethiopian Federal High Court’s July 18 decision to press charges against six bloggers and three independent journalists under the Anti-Terrorism Proclamation.
We urge the Ethiopian government to ensure that the trial is fair, transparent, and in compliance with Ethiopia’s constitutional guarantees and international human rights obligations. We also urge the Ethiopian government to ensure that the trial is open to public observation and free of political influence.
We reiterate Secretary Kerry’s May 1 call on Ethiopia to refrain from using anti-terrorism laws as a mechanism to curb the free exchange of ideas. The use of the Anti-Terrorism Proclamation in previous cases against journalists, activists, and opposition political figures raises serious questions and concerns about the intent of the law, and about the sanctity of Ethiopians’ constitutionally guaranteed rights to freedom of the press and freedom of expression.
Freedom of expression and freedom of the press are fundamental elections of a democratic society. The arrest of journalists and bloggers, and their prosecution under terrorism laws, has a chilling effect on the media and all Ethiopians’ right to freedom of expression.
The Office of Website Management, Bureau of Public Affairs, manages this site as a portal for information from the U.S. State Department.
External links to other Internet sites should not be construed as an endorsement of the views or privacy policies contained therein.
Monday, 14 July 2014
Sunday, 13 July 2014
አብርሃ ደስታ – ከትግራይ አዲስ አበባ ማዕከላዊ እስር ቤት ገባ
(ኢ.ኤም.ኤፍ) በትግራይ የሚደረጉ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በመጻፍ እና በመተቸት ይታወቃል – አብርሃ ደስታ። በትጋይ የሚገኙት ሰዎች የአብርሃ ደስታን ሃሳብ – በሃሳብ ማሸነፍ ሲያቅታችው አስረውታል። ከታሰረ በኋላ ወዴት እንደተወሰደ ለማወቅ አልተቻለም ነበር። ዛሬ ያገኘነው መረጃ ግን አብርሃ ደስታ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ ማዕከላዊ እስር ቤት ተዛውሮ እንደሚገኝ ለማወቅ ችለናል።\
ይህ በ እንዲህ እንዳለ፤ በሚቀጥለው ሳምንት እሁድ በራያ እና አዘቦ የሚደረገውን የአረና ፓርቲ ስብሰባ፤ “ዘመቻ አብርሃ ደስታ” ማለታቸውውን አሳውቀዋል። አረና የትግራይ ፓርቲ እንደገለጸው ከሆነ፤ ዓረና-መድረክ እሁድ 06 / 11 / 2006 ዓ/ም በራያ ዓዘቦ ወረዳ ሞኾኒ ከተማ “ዘመቻ ኣብረሃ ደስታ” የሚል መፈክር ያለበት ህዝባዊ ስብሰባ ያካሂዳል።
ዓረና-መድረክ ፖሊሲው፣ ስትራተጂውና ኣማራጭ ሃሳቡ ከራያ ዓዘቦና ኣከባቢው ህዝብ ለመወያየትና ለማስተዋወቅ ህዝባዊ ስብሰባ ጠርተዋል።
ዓረና-መድረክ የሃገራችን የፍትህ፣ ዲሞክራሲ፣ መልካም ኣስተዳደር፣ ሁላቀፍ ልማት፣ የሚድያ ነፃነት፣ ወዘተ ተግዳረቶች በማቅረብ ለነዚህ ችግሮች መፍትሄ ኣማራጭ ሃሳቦች በማቅረብ ወደፊት ሃገራችን የምትመራበት ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ምን መምሰል እንዳለበት፣ ሰለማዊ የስልጣን ሽግግር እውን የሚሆንበት ኣግባብ፣ ባለፈው 17 የትጥቅ ትግል የተከፈለ መስዋእትነትና በኣሁኑ ሰዓት የተገኘው ለውጥ ምን እንደሚመስል ከራያ ህዝ ጋብ እንወያያለን።
Friday, 11 July 2014
አብርሀ ደስታ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ ፍርድ ቤት ቀረበ
ካሳለፍነው ማክሰኞ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስት ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር ውለው በማዕከላዊ በእስር ላይ የሚገኙት ወጣቱ ፖለቲከኛ ሀብታሙ አያሌው የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ፣ ወጣቱ ፖለቲከኛ ዳንኤል ሺበሺ የአንድነት ፓርቲ ድርጅት ጉዳይ ም/ሀላፊ ወጣቱ መምህርና ፖለቲከኛ አብርሃ ደስታ የአረና ፓርቲ አመራር በትላንትው ዕለት ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ቢጠበቅም ከምሽቱ 12፡16 ላይ የአረና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አብርሃ ደስታ ብቻውን በ3 ፌደራል ፖሊሶች ታጅቦ ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡ ማንም ወደ ፍርድ ቤቱ እንዳይገባ በፀጥታ ሀይሎችና ሲቪል በለበሱ የደህንነት ሀይሎች በመከልከሉ ምክንያት ስለቀረበበት ክስ ለማወቅ ያደረግነው ጥረት ሊሳካልን አልቻለም፡፡ በወጣቱ ፖለቲከኛ አብርሃ ደስታ ፊት ላይ ይታይ የነበረው ጉስቁልና ከፍተኛ የሀይል እርምጃዎች ሳይወሰድበት እንዳልቀረ አመላካች ነበር፡፡ ይህንን ዜና እስካጠናቀርንበት ጊዜ ድረስ የአንድነትና ሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ፍርድ ቤት አልቀረቡም፡፡
Sunday, 6 July 2014
Ambo University fires one of the detained Zone 9 bloggers, lecturer Zelalem
The letter, dated July 02, 2014, posted on Ambo University’s staff notice board states that Zelalem Kibert Beza, lecturer at the University and a member of the blogging collective, Zone 9, has been officially fired from his post as he “had not responded to two previous calls witten within the past couple of months to report about his absence from the University.”
Zelalem was detained on the April 25, 2014 along with eight other bloggers and journalists in Addis Abeba accused of various anti-government plots. He has not been yet charged. Police has been holding Zelalem for the past three months without officially charging him but bringing him to court and seeking further time to conduct investigation.
Signed by Dr. Lakew Wondimu Abachri, the Academic and Research Deputy President of Ambo University, the letter (attached below) also orders Zelalem to return all materials and works he has been handling back to the University. The letter has been copied to various administrative offices and departments of the University.
Wednesday, 2 July 2014
የኢትዮጵያ ህዝብ በዝምታ እየተቀበላቸው የሚገኙት በደሎች
ያሳዝናል! በአመት ከ70 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ህፃናት በማደጎነት ሲሸጡ እያየን፣ እየሰማን፤ ከ45 ሺህ በላይ ሴቶቻችን ለሳውዲ አረቢያ በቤት ሰራተኝነት ሲቸረቸሩና፤ ቁጥር ስፍር የሌላቸው ዜጎቻችን በተመሳሳይ መልኩ ለሌሎች አረብ ሃገራት በሃራጭ ሲሸጡ እያየን፣ እየሰማን፤ ሴቶቻችን በየ አረብ ሃገሩ ለመስማት እጅግ በሚያዳግት ሁኔታ አሰቃቂ በደሎች ባደባባይ ሲፈፀምባቸው እያየን፣ እየሰማን፤ አያሌ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ህይወታቸውን ለማትረፍና ለማሻሻል ወደተለያዩ ሃገራት ተሰደው ስቃይ ውስጥ እንደሚገኙ እያየን፣ እየሰማን፤ ከዚህም በላይ ደግሞ ይህ ሁሉ በደል በዜጎች ላይ ሲፈፀም ቢያንስ ተቃውሞውን ሊያሰማ ፈፅሞ ፍላጎት የሌለው፤ ይባስ ብሎ በደሉን በተቃወሙ ዜጎች ላይ ከበዳዮቹ ሃገራት ጋር በማበር ንፁሃን ዜጎችን የሚደበድብ፣ የሚያስር ጭካኝ ስርዓት በጫንቃችን ተሸክመን፤ አንጀታችን እያረረ፣ ልባችን በሃዘን እየተጎዳ፣ ሞራላችን በውድቀት እየተሰበረ፣ አንገታችንን ደፍተን በዝምታ እየኖርን እንገኛለን።
ሁላችንም እንደምናቀው የኬኒያ፣ የሱዳን፣ የጅቡቲና፣ ሌሎች የጎረቤት ሃገራት በወያኔ በደል ምክንያት ሳይወዱ ተገደው ህይወታቸውን ለማዳን ከሃገራቸው በተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ላይ በተደጋጋሚ አፈና እየፈፀሙ ይገኛሉ። በቅርቡ በኬኒያ መንግስት ታፍኖ ለወያኔ ከተሰጠ በኋላ ህይወቱ እስክታልፍ ድረስ ለአመታት በወያኔ እስር ቤት በተሰቃየው በወንድማችን ወጣት ተስፋሁን ጨመዳ ላይ የተፈፀመውን አሳዛኝ በደልና በኦብነግ አመራር አባላት ላይ የተደረገው አፈና፤ በደቡብ ሱዳን በአቶ ኦኬሎ አኩአይና ሌሎች የጋምቤላ ንቅናቄ አባላት ላይ በተመሳሳይ መልኩ የተደረገው አፈና ያለምንም ተጨባጭ እርምጃ በዝምታ ታልፈዋል። ዛሬ ደግሞ የየመን መንግስት በአሳዛኝ ሁኔታ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ማገቱ በመገናኛ ብዙሃን ተነግሯል።
በዜጎቻችን ላይ እየደረሱ ለሚገኙት አሰቃቂ በደሎች በዋነኝነት ተጠያቂው የወያኔ መንግስት ቢሆንም፤ በስደት የሚኖሩ ዜጎቻችን ላይ ከወያኔ መንግስት ጋር በመተባበር በተደጋጋሚ አፈና እየፈፀሙና አጋልጠው እየሰጡ የሚገኙ የጎረቤት ሃገራት ወደፊት በኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ተጠያቂ እንደሚሆኑ ምንም ጥርጥር የለኝም። ነገር ግን ወገኖቼ ይህ አፈና እስከመቼ ይቀጥላል!? ዜጎች ጭቆናን በመቃወማቸው ብቻ በስደት ከሚደርስባቸው ስቃይ በላይ ለምን በየ ጎረቤት ሃገሩ ይታፈናሉ!? እኛ ኢትዮጵያውያን እስከመቼ እየተናቅን እንኖራለን!? ጎበዝ ዝምታውና መነጣጠሉ ይብቃ! የሚደርስብንን አፈና ለማስቆምና ራሳችንን ለመከላከል ሁላችንም በአንድነት ጫና መፍጠርና ማስገደድ ግድ ስለሚለን፤ በምንችለው ሁሉ መረባረብና መተባበር ይኖርብናል እላለሁ።
አፈናው ይብቃ!
Subscribe to:
Posts (Atom)